መግቢያ » ልዩ ልዩ ሁለት » ለእኔ ነው ! ?

የትምህርቱ ርዕስ | ለእኔ ነው ! ?

አዎ ጌታዬ ለእኔ ነው ዘመን የጨመርከው? ለእኔ ነው እያጡ ማግኘትን፣ እየሞቱ ሕያው መሆንን ያደልከው ? እኮ አንተ የቀትሩ ጥላ፣ አንተ የበረሃው ምንጭ ለእኔ ነው የመኖር ፈቃድ የሰጠኸው? በዚህ በጥም ቀን ለእኔ ነው የደረስከው? ከተሰበከው፣ ከተዘመረው በላይ የሆንከው፣ የበላይ የሌለብህ የበላይ ሆይ ለእኔ ነው ፍቅርህን የላከው? ሰውን መዓት ያስደነግጠዋል፣ ራሱ የሚያንስበት አሽከር ግን ውለታ ያስደነግጠዋል። እኮ ያልጠበቅሁትን ቀን፣ አይደርስም ያልኩትን ዓመት አየሁት ! አንተ የዕድሜ ማማ፣ አንተ ዝርግፍ ጌጥ፣ አንተ በራስህ የምትኖር፣ አንተ የጠላት ብዛት የማይመልስህ እግዚአብሔር ሆይ ተመስገን! በከፍታም በዝቅታም ለታመኑልኝ ወዳጆች ክብረት ስጥልኝ! በአማኑኤል ስምህ፣ በፈሰሰው ደምህ ፣ በማርያም እናትህ ! አሜን።

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ታኅሣሥ 1 ቀን 2017 ዓ.ም.

በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም