የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ

የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ 

መስቀል ቅዱስ ኤፍሬም /306-373 ዓ.ም./ እንደሰበከው

እንኳን ለ2011 ዓ.ም የመስቀል በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ !
መስቀል የጣዖት አምልኮን አጠፋ። ለዓለም ሁሉ በማብራት ሁሉንም ዝብ ወደ አንዲቷ ቤተ ክርስቲያን በመሰብሰብ በፍቅር አንድ አደረጋቸው
         መስቀል የሙታን ትንኤ ነው
         መስቀል ለክርስቲያኖች ተስፋ ነው
         መስቀል ለሽባው ምርኩዝ ነው
         መስቀል ለድው አጽናኝ ነው
         መስቀል የትዕቢተኛው መጥፊያ ነው
         መስቀል ተስፋ ለቆረጡ ተስፋ ነው
         መስቀል በባር ለሚጓዙ/ለመርከበኞች ምግብ ነው
         መስቀል ለአውታታዎች መሸሸጊያ ነው
         መስቀል ለድሀ አደጎች አባት ነው
         መስቀል ለተኞች መጽናናት ነው
         መስቀል የፃናት ጠባቂ ነው
         መስቀል የሰው ልጅ ክብር ነው
         መስቀል የሽማግሌዎች አክሊል ነው
         መስቀል በጨለማ ለሚኖሩት ብርሃን ነው
         መስቀል ለባሮች ነጻነት ፣ ላልተማሩ ጥበብ ነው
         መስቀል የነቢያት ስብከት ፣ የሐዋርያት የመንገድ ጓደኛ ነው
         መስቀል የልጃገረዶች ድንግልና ፣ የካህናት ደስታ ነው
         መስቀል የቤተ ክርስቲያን ብሎም የዓለም መሠረት ነው
         መስቀል የአብያተ ጣዖታት ውድመት ፣ የአይሁዳውያን ፈተና ነው
         መስቀል የለምሞች መንጻት ፣ የደካሞች ብርታት ነው
         መስቀል ለተራቡ እንጀራ ፣ ለተጠሙ ምንጭ ነው
         መስቀል የመነኮሳት መልካም ተስፋ ፣ ለተራቆቱት ልብስ ነው
በዚህ ቅዱስ መሪያ ጌታችን ክርስቶስ ሁሉንም ይውጥ የነበረውን የሲዖልን አንጀት አራቆተ በዲያብሎስ አፍ ያሉትን ብዙ ወጥመዶችም ዘጋ። መስቀልን ተመልክቶ ሞት ፈራ ከአዳም ጋር አብሮ ይዞ የነበረውን ሁሉፍጥረት ለቀቀ ። እግዚአብሔርን የተሸከሙ ሐዋርያት መስቀልን ታጥቀው የጠላትን ሁሉንም ኃይል ድል አደረጉ ሰውን ሁሉም በመረባቸው አጠመዱ። የተሰቀለውንም እንዲያመልኩ ሁሉንም አንድ ላይ ሰበሰቡ ። (ወታደሮች) በጦር መሪያ እንደሚታጠቁት የክርቶስ ሰማዕታት የአሳዳጆችን ዕቅድ ሁሉ ድል አደረጉ ። በግልጽም መስቀል የተሸከመውን አምላክ ሰበኩ። ለክርቶስ ብለው መስቀሉን ተሸክመው በዓለም ያለውን ሁሉንም ነገር ካዱ በበረሃና በተራራ በዋሻ ኖሩ ዓለምንም እቢ አሉ
ነገር ግን ይህ የማይበገር የኦርቶዶክስ ግንብ ፣ የሰማያዊው ንጉየድል መሪያ የሆነውን መስቀሉን ለማመስን የተገባ ቋንቋ እንዴት ያለ ነው !? ኃያሉ ጌታ በመስቀል  በቃላት የማይገለጥ በረከትን ለሰው ልጆች ሰጠ
ስለዚህ በግንባራችን ፣ በዓይናችን ፣ በአፋችንና በደረታችን ላይ ይወት የሚሰጠውን መስቀል እናስቀምጥ ። (እነዚህን አካሎቻችንን) የክርስቲያኖች የማይበገር መሪያ ፣ የአማኞች ተስፋ ብርሃን በሆነው በመስቀል እናስጊጣቸው በዚህ የኦርቶዶክስ እምነት ምርኩዝ ፣ አዳኝ ሆነውበቤተ በክርስቲያን ምስጋና መሪያ ገነትን እንክፈት ። ለአንድ ሰዓትም ይሁን ለአንዲት ቅጽበት መስቀልን አንርሳ ያም ያለ መስቀል አንዳች አናድርግ ። ነገር ግን እንቅልፍ ስንተኛ ሆነ ስንነ፣ ስንራ ሆነ ስንመገብ ወይም ስንተኛ ፣ መንገድ ስንጓዝሆነ በባር ስንሄድ አያም ወንዝ ስናቋርጥ የአካል ክፍሎቻችንን ሁሉ ይወት ሰጪ በሆነው መስቀል እናስጊጥ ። “ከሌሊት ግርማ ፥ በቀን ከሚበርር ፍላጻ በጨለማ ከሚሄድ ክፉ ነገር ፥ ከአደጋና ከቀትር ጋኔን” (መዝ 90(91)፥5-6) አንፍራ ። ኦ! እናንተ ክርስቲያኖች ሁልጊዜ የክርስቶስን መስቀል እንደ ረዳትና አጋዥ ከጎናችሁ ከያዛችሁ የሚቃወመን ኃይል ይቶት ይርዳል ይሸሽማልና  “ዲያብሎስ ወደ እናንተ አይመጣምአንዳች መቅሰፍትወደ መኖሪችሁ አይገባም ።”
ለዘላለሙ አሜን !
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ
አዳዲስ መጻሕፍትን ይግዙ

ተዛማጅ ጽሑፎች

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ