መግቢያ » ግጥም » መንፈሱና ሙሽራይቱ

የትምህርቱ ርዕስ | መንፈሱና ሙሽራይቱ

                               ሐሙስ፣ መጋቢት 13 2004 ዓ.ም.
ደግ ሰው አልቆ ጉብዝናም ሠሎ
መተማመን ክብርዋ ጎድሎ
ፍቅር ቀዝቅዛ
 ጽድቅ አዘቅዝቃ
እውነት ጠንዝቶ
በረከት ጠፍቶ
ስለተፈታ ያ አንድነቱ
ና ትልሃለች ሙሽራይቱ።

በአሳዳጆች ጉልበት

 በከሳቾች ጩኸት
በሥጋ ደም ምክር
 በጅብ እርሻ ፍቅር
ጀርባችን ጎብጦብን
ልባችን ርዶብን
ሰልችቶናልና ተስፋ የፍጥረቱ
 ናልን በምሕረት በቶሎ አቤቱ።
የጨለማ ጮራ
 አጉርሶ ካራ
የቀኑ ድቅድቅ
 ፍትፍትና ምርቅ
አፍቅሮ ከሳሽ
 ቀድሶ አርካሽ
የማንጨበጥ ሙልጭልጭ ድንጋይ
ሆነናልና ቅዱስ አዶናይ
ና ና ሰብስበን በየፈርጃችን
መንፈሱ እና ሙሽራይቱ ና ና ይሉሃል ና ናፍቆታችን።
ሙሽራይቱ ና ትልሃለች
በውብ አጊጣ ደጅ እየጠናች
ና ና ይልሃል መንፈስ ቅዱስም
በብዙ ደስታ የተዋቡትን
             የበጉን ልጆች በክብር እንድትሾም።
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም