መግቢያ » ግጥም » ማየቴ አያምንም

የትምህርቱ ርዕስ | ማየቴ አያምንም

                               ረቡዕ፣ ኅዳር 13 2004

ከመቃብር፤ከተማሰው ጉድጓድ ማዶ
ከሚታየው፤ ከዚህ ዓለም ትንሽ ጎጆ
ከጨለማ ወዲያ ከሞትም ባሻገር
ተስፋዬ እዛ ነው ከሰማያት አገር፡፡

ተስፈኛ አይደለሁም ከፍጡር እንጀራ
ከትዳር ከሀብቱ ከስልጣኑ ተራ
አላስብም ከቶ ነገድና ዘሬን
ለጌታ ያልሆነ ችሎታ እውቀቴን
ተስፋ ከምድር የለም ከሰዎች መካከል
ሚጨበጥ ሚዳሰስ የሚታይም አይደል፡፡
ተስፋዬም ረዳቴም ከላይ ነው ከሰማይ
ሣምነው ማየው እንጂ አይደለም የሚታይ
ሩጫዬን ሮጣለሁ በወደደኝ በእርሱ
በአይኖቼ አያለሁ ሙታን ሲነሱ
ወዲያ ነው ተስፋዬ በአይን አይታይም
አመስጋኝ ነኝና ማመኔ አይዝልም
ማየቴ አያምንም ማመኔ ግን ያያል
ልቤ ከተስፋዬ በሰማያት አርፏል፡፡
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም