ጌታ ሆይ እነዚህ ውብ ድምፆች ፣ ባሪያህ ኢዮብ መከራ ስቃይ በበዙበት ወቅት እንዲናገራቸው የሰጠኸው ቃላት ናቸው ። እነዚህን ቃላት እንደ እኔ ባለ ኃጢአተኛ አፍና ልብ ላይ እንደገና አስቀመጥህ ። እንዴት ያለህ መልካም ነህ ! አንተ አንድ ወቅት ጤናን ሰጠኸኝ እኔም ረሳሁህ ። አንተም (ጤናዬን) ከእኔ ወሰድህና አሁን ወደ አንተ ተመለስሁ ። እንዴት ያለ እጅግ ታላቅ ስጦታ ነው ! ራስህን ለእኔ ትሰጠኝ ዘንድ ካንተ ይለዩኝ የነበሩትን ያንተን ስጦታዎች ከእኔ አራቅሃቸው ።
ጌታ ሆይ ፣ ካንተ ያልሆነውን በእኔ ያለውን ሁሉንም ነገር ውሰድ ። ሁሉም ነገር ያንተ ነው ። አንተ ጌታ ነህ ። ምድራዊ መልካም ነገሮችን ፣ ክብር፣ ጤና ፣ ሕይወት ሁሉንም ነገር እዘዝ ። በእኔ ውስጥ ያንተን ቦታ የሚወስደውን ሁሉንም ነገር ከሥሩ ቊረጠው።