የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ

የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ 

ሰማያዊ ወግ / 9

የምእመኑ ድምፅ!

ጌታ ሆይ ! በቀንና በሌሊት ወዳንተ እጮኻለሁ ፣ ዝም ብትለኝ ከቆሙት በታች ፣ ከሞቱት በላይ እሆናለሁ። በነፍስ ግሥጋሴ ወዳንተ እመጣለሁ ። በልቤ አለህ ፣ አንተን አስሳለሁ ። አጠገቤ አለህ፣ ግን እፈልግሃለሁ ። ከእኔ አልራቅህም ፣ ነገር ግን ሀልወትህ ይሠወረኛል ። በሥራህ እየተናገርህ ነው ፣ እኔ ግን በቃል ዝም አለኝ እልሃለሁ ። አንተን በቀንና በሌሊት ፍርርቅ ውስጥ ካላየሁህ በምን ውስጥ አይሃለሁ? እስትንፋሴን ደግፈህ በመያዝህ ካላመሰገንሁህ በምን አመሰግንሃለሁ? በውስጤ እያለህ በደጅ ስፈልግህ እኖራለሁ።

አንተን ጌታዬን በታሪክ ጅረት ውስጥ አላስስህም ። በመዛግብት ውስጥ አልበረብርህም :: በሕይወቴ አደባባይ በፍቅር ፣ በኑሮዬ ዐውድ በበረከት ስትገለጥ አስተውላለሁ ። አያለሁ ፣ ግን አላይም ። እመለከታለሁ ግን አላስተውልም ። በማጣት ውስጥ ማግኘት ሲሰማኝ እርሱ እምነት ነው ። በማግኘት ውስጥ ማጣት ሲሰማኝ ፣ በረከቴን በአፌ ይዤ ራበኝ እያልሁ ሳጉረመርም እርሱ አለማመን ነው ። አማኑኤል ሆይ እንደ ንሥር ክንፍ እጆችህን በመስቀል ላይ የዘረጋኸው አለማመኔን እርዳው ! ወደ እቅፍህ ሰብስበኝ ! ዝናን በተሞላው ስምህ አሜን !

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ተፃፈ ግንቦት 17 ቀን 2015 ዓ.ም.

በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ
አዳዲስ መጻሕፍትን ይግዙ

ተዛማጅ ጽሑፎች

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ