የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ

የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ 

ቅዱስ ጎርጎርዮስ ገባሬ መንክራት ዘላለማዊ ድንግል ቅድስትም ስለ ስለሆነችው ስለ ወላዲተ አምላክ የሰበከው ስብከት /2/

ያ ሰውን ከድንግል መሬት የፈጠረው ራሱ አሁንም ልክ እንደዚያ ያደርጋል
ልክ በአበባ ጉንጉን ላይ እንዳለው የራሳችንን ነፍስና ስለ በሉ ማድመጥ የሚወዱት ነፍሶች ከወርቃማው አበባ /ከክርስቶስ/ ጋር እናዋህድ ። ከማይጠወልገው የአትክልት ቦታ አክሊልን ለመድፋት እንዘጋጅ። የክርስቶስንም አበባዎች በእጃችን ለማቅረብ እንሰብስባቸው። የሚያበራው ድ ሉል ወደ ጨለማና ወደ ሞት ጥላ ይሄዱ የነበሩትን ደማቅ ወደሆነው ዘላለማዊ ብርሃን ያወጣቸው ዘንድ ከእርሷ ወጥቷልና እግዚአብሔርን የሚመስለው የቅድስት ድንግል ማፀንም እንዲህ ባለ አክሊል ይጌጥ ዘንድ ይገባል ። 
መለኮታዊ በሆኑት በክርስቶስ ቃላት ሴት አድርገን መልካም የሆነውን ዝማሬ እናቅርብለት ። የያውነት ምጢር የሆኑትን ፍሬዎች ለመሰብሰብ እንፋጠን ። እግዚአብሔር የተዋሐደውን (መልካም) መዓዛ ለማሽተተ እንፋጠን ። በእኛ ቋንቋ እንደምንለው በመለኮታዊው ጸጋ እንደሰትየሚከረፋውንም የኃጢአት ሽታ ከራሳችን ለማራቅ እንፋጠን። ከዚህ ይልቅ ጣፋጭ በሆነው በጽድቅ ሥራ ራሳችንን እናልብስ። የእምነትን ጋሻ ይዘን የመልካም ሥራ ልብስንም ለብሰን ፣ ቅዱስና ነቀፋ የሌለበትንም የንጽሕናን ዝናር ታጥቀን እንጹም ። እርሱ ከፍ ያለ ነው መኖያውም ከሰላም ጋር ነው። ኦ! ወዳጆቼ ሆይ እኛ ግን በአዳኙ የአትክልት ስፍራ አርፈን በመለኮታዊው ጸጋ ቋንቋ ከመላእክት ጋር ሁነን ቅድስት ድንግልን “ደስ ይበልሽ ሴትም አድርጊ” እያልን እናመስግናት ። ከእርሷ መጀመሪያ በመልካምነቱ የሚያበራልን ዘላለማዊው የብርሃን ነፀብራቅ ወጥቷልና
ቅድስት ድንግል ራሷ የተከበረች የእግዚአብሔር ቤተ መቅደስና የነች ሳጥን ፣ ሁሉም የሚቃጠሉት መዋዕቶች የሚቀርቡባት የወርቅ መዊያ ነች ። እጅግ በላቀውና ልዩ በሆነው ንጽሕናዋ ምክንያት ለፈጣሪ የምትቀርብ ዕጣን ቅዱስ የሆነው ጸጋ ቅባትነተኛውን ናርያዘች ውድ ማሰሮ ፣ የእግዚአብሔርን ስታ የሚገልጽ ክህነታዊ ወደሆነው የወርቅ አክሊል  የምትቀርብ በሥጋና በነፍስ ንጽት የሆነችው እርሷ ብቻ ነች ። ወደ ምራቅ የዞረችው በር እርሷ ነች ከእርሷ በወጣው (ብርሃን) ምድር በራ ። መንፈስ ቅዱስ ከእርሷ አዳኙ የተዋሐደውን ሥጋ የወሰደባት የለመለመች የወይራ ዛፍ እርሷ ነች ። እርሷ የደናግላን መመኪያ የእናቶች ደስታ ነች “ደስ ይበልሽ ፥ ጸጋ የሞላብሽ ሆይ ፥ ጌታ ከአንቺ ጋር ነው” (ሉቃ. 1 28) ተብሎ እንደ ተነገረው የመልአአዋጅ በኃጢአት ምውት የነበሩትን ያድስ ዘንድ ከእርሷ ተወለደ
ኦ! ጌታ በማፀኗ ታድር ዘንድ አስቀድመህ ሊቀ መላእክት እንዲያበራት አድርገህ ድንግልና ደስተኛ እንድትሆን ፈቀድህ ። ነገር ግን ከላይ ቅዱሳን ከሆኑት ሰማያዊ አገልጋዮች የሆነውገብርኤል ወደ ማርያም መጣና እንዲህ የሚለውን የምራች አበሰራት “ደስ ይበልሽ”እንዲህም ብሎ ጨመረ “ጌታ ከአንቺ ጋር ነው፤ አንቺ ከሴቶች መካከል የተባረክሽ ነሽ አላት ።” (ሉቃ. 1፥28)። ነገር ግን እርሷ በውስታውካ ይህ እንዴት ያለ የምራች ነው ብላ አሰበች ። እርሷ በሁሉም መንገዶች ጠቢብ ከሴቶችየሚመስላት የለምና እኔም እንደዚሁ ቅድስት ድንግልን የመረጣትን ጸጋ አስባለሁ
በገነት ብቻዋን እ ነበረችው ክፉ የነበረውን የእባቡን ወሬ ሰምታ የልሳብ እንደ ጣለች፣ የቅዱሱን ድካምና ዘን ንዳመጣችው እንደ መጀመሪያይቱ ድንግል አደለችም ። ቅድስት ድንግል ግን እንዲህ ነበረችበእርሷ የቀደመው መተላለፍ ተደመሰሰ። ሣራ እንዳደረገቸውም ልጅ ትወልጃለሽ የሚል የምራች ስትሰማ አልሳቀችም ። አያም ልክ እንደ ርብቃ አታላይ እንደሆነ ሰው በብስጭት ጌጥ ተቀብላ ለእጮኛዋ ግመሎች ውአልሰጠችም ። እንደ ሌሎች ሴቶችም (የመልአኩን) ሰላምታ ዝም ብላ አልተቀበለችም ነገር ግን ብሩህ በሆነ ሳብ መርምራ እሺ አለች ፡-
እንዲህ ያለን በረከት ከወዴት ነው ያመጣኸው ? እንዴት ካለ ግምጃ ቤትስ ነው የዓለም ሉል (ክርስቶስ) የተላከ? ስጦታው ምን እንደሆነ (አካላዊ) ቃልንም የተሸከመው ማን እንደሆነ ማወቅ እፈልጋለሁ ያም ላኪው ማን እንደሆነ ማወቅ እፈልጋለሁ
እነዚህን ነገሮች ቅድስት ድንግል በውስጧ በጥርጣሬ ጠየቀች ። ነገር ግን መልአኩ እንዲህ ባሉ ቃላት ጥርጥሯን አራቀው ፡- “መንፈስ ቅዱስ በአንቺ ላይ ይመጣል፥ የልዑልም ኃይል ይጸልልሻል ስለዚህ ደግሞ ከአንቺ የሚወለደው ቅዱስ የእግዚአብሔር ልጅ ይባላል ።  (ሉቃ. 1 35)  ልጅም ትወልዳለች፤ እርሱ ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ (ማቴ 1፥21)
ድንግልም ለመልአኩ እንዲህ ብላ መለሰችለት፡-ዋናተኛ ር ላይ እንደሚዋኘው ሳቤ በተናገርሃቸው ቃላት ውስጥ እየዋኘ ነው ። ይህ እንዴት ይሆንልኛል ? ራሴን ለሰማያዊው ሙሽራ ሰጥቻለሁና ምድር ላይ ወንድን ማወቅ ፈጽሜ አልሻም። ድንግል ሆኖ መኖርን እወዳለሁ የድንግልናዬንም ክብር ማጥፋት አልፈልግም ።”
እንዲህ ያሉ ቃላትን ብትናገርም መልአኩ ቅድስት ድንግልን እንዲህ ብሎ አረጋገጠላትማርያም ሆይ የመጣሁት ላስፈራሽ ሳይሆን ፍርሃትሽን ለማስወገድ ነውና አትፍሪ ። ማርያም ሆይ በእግዚአብሔር ዘንድ ጸጋን አግኝተሻልና አትፍሪ ። ከተፈጥሮ ግ በታች አይደለምና (የእግዚአብሔርን) ጸጋ አሳንሰሽ አትመልከቺ። መንፈስ ቅዱስ ባንቺ ላይ ይመጣል ስለዚህ ካንቺ የሚወለደው የመልኩና የባርይው ብሎም የዘላለማዊነቱ ተካፋይ የሆነው ቅዱሱ የእግዚአብሔር ልጅ ነው
ኦ! ማርያም ሆይ የተማርው ምጢር እጅግ ታላቅ ነው ። ይህም ምጢር አሁን ድረስ ከመላእክት የተሰወረ ነው ። አንቺ ነያትና አባቶች ያልሰሙትን ሰምተሻል ። አንቺ የእግዚአብሔር መዘምራን እንኳን ሊሰሙ ያልተገባቸውን ሰምተሻል። ዳዊት ኢሳይያስና ሌሎችም ነያት በስብከታቸው ጌታ ሰው እንደሚሆን አስቀድመው ተናገሩ። ኦ! ቅድስት ድንግል አንቺ ብቻ ከእነርሱ የተሰወረውን ምጢር ተቀበልሽ ። ስሚ ይህም (ምጢር) አንቺ ላይ እንዴት እንደሚፈጸም ግር አይበልሽ ። ያ ሰውን ከድንግል መሬት የፈጠረው ራሱ አሁንም ልክ እንደዚያ ያደርጋል ። ለፍጥረቱ ድኅነት ያደርገዋል
የዘላለማዊው ብርሃን ነፀብራቅ በእነዚህ ቃላት አሁን ይበራልናል ። በእርሷ ሁሉም የነፍስ ብቶች አሉ ፤ ሕያውም የሆኑ ናቸውና ከሁሉም አስቀድሞ ጥበብ በተሞላበት መልኩ “ደስ ይበልሽ” (ሉቃ. 1 28) ብሎ መልአኩ ያመሰገነውን የድንግልን ማንነት ማድነቅ ለእኔ ግድና ተገቢ ነው። ከዓለም/ከሴቶች በሙሉ ወንድ ሳታውቅ ድንግልና እናት የሆነችው ፣ በሥጋም በነፍስም ቅድስት ሁና የተገኘችእርሷ ብቻ ናት ። ከዓለም/ከሴቶች በሙሉ እግዚአብሔርን ለመውለድ የተገባች እርሷ ናት ። ሁሉንም በቃሉ የሚሸከመውን/ደግፎ የሚይዘውን የተሸከመው እርሷ ብቻ ናት
ቅድስት የሆነችው የአምላክን እናት በውበቷ ብቻ ሳይሆን በመንፈሷ ታላቅነትም ማድነቅ የሚገባ ነው “እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ነው” “ጌታም ካንቺ ይወለዳል” እንዲህ የሚለው ቃል የተነገራት በዚህ ምክንያት ነው እንደ መለኮታዊ ምሥጢር መዝገብነትዋ ቅድስት ድንግል ራስዋን አዘጋጀች፣ የሕይወት ሉል ክርስቶስም በሥጋ በውስጥዋ ተሰወረ ። እርሷም ከተፈጥሮ በላይ ታላቅ የሆነው የመለኮታዊ ድኅነት መንበር ሆነች
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ
አዳዲስ መጻሕፍትን ይግዙ

ተዛማጅ ጽሑፎች

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ