የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ

የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ 

ቅዱስ ጎርጎርዮስ ገባሬ መንክራት ዘላለማዊ ድንግል ቅድስትም ስለ ስለሆነችው ስለ ወላዲተ አምላክ የሰበከው ስብከት /1/

እንኳን ለጾመ ፍልሰታ አደረሳችሁ !
ከእርሷ በመልካምነቱ የሚያበራልን ዘላለማዊው የብርሃን ነፀብራቅ ወጥቷልና። ኦ! ወዳጆቼ ሆይ እኛ ግን በአዳኙ የአትክልት ስፍራ አርፈን በመለኮታዊው ጸጋ ቋንቋ ከመላእክት ጋር ሁነን ቅድስት ድንግልን “ደስ ይበልሽ ሴትም አድርጊ እያልን እናመስግናት”
ዋንን አለመታዘዝ ሳስብ አለቅሳለሁ ። ነገር ግን የማርያምን ፍሬ ስመለከት እንደገና እታደሳለሁ ። በባርይህ የማትሞት ፣ ከውበትህ የተነስውር የሆንህ ፣ ከዘመናት በፊት[1]ከብርሃን የተገኘብርሃን አንተ ከእግዚአብሔር አብ ተወለድህ ። (አካላዊ) ቃልና የእግዚአብሔር ልጅ ሆነህ ሳለ በተቀደሱ እጆህ የተበጀውን አዳምን አዲስ አድርገህ ታድሰው ዘንድ ከድንግል ማርያም ሥጋን ነ
ቅዱስ ፣ የማትሞት ፣ ዘላለማዊ ፣ የማይደረስብህ ፣ የማትቀየር ፣ የማትለወጥ ፣ ከዘመናት በፊት እውነተኛ የእግዚአብሔር ልጅ የሆንከው አንተ በቅድስት ድንግል ማፀን መጸነስደስተኛ ነበርህ ። ይህንንም ያደረግው በተቀደሱ እጆህ የተበጀውን በኃጢአትም የሞተውን ሰው ያው ታደረገው ዘንድነው
በማይታየው በአባትህ ፈቃድና ስምረት ወደዚህ ዓለም መጣህ ። ስለዚህ ሁላችንም ንጉችን ብለን እየጠራን እንለምንሃለን ። ረዳታችን የሆንው ፣ ከድንግል የተወለድው በመጠቅለያም ተጠቅልለህ በበረት የተኛው ፣ የማርያምንም (ጡቶች) የጠባኸው አንተ የመጀመሪያ ሰው የሆነውን በኃጢአትም የሞተውን አዳም ያው ታደርገው ዘንድ (ይህን አደረግህ)
ከመለኮታዊው እውቀት እውቀትን ተካፍለን ልክ እንደ ምንጭ ጣጭ ሆኖ የሚደመጠውን የምስጋና መዝሙር እናፍልቅ ። ጣፋጭ በሆኑ ትምህርቶች ለመለኮታዊው ጸጋ የሚባውን ምስጋና እንስጥ ። የእርሱ ኃይልና ግርማ በእኛ መካከል ነበርና በዚህም ምክንያት ምድር ፣ ባር ፣ የሚታዩትና የማይታዩት ፍጥረቶች በሙሉ እግዚአብሔር ለሰው ያለውን ፍቅር ያመሰግናሉ ያከብሩማል ። በፍጻሜው ባለ መታዘዝ ምውት ሆኖ የነበረውን (አዳምን) አዲስ አድርጎ ያድሰው ዘንድ እርሱ አምላክ ሆኖ ሳለ በሥጋ ተገለጠ።  ፍጹም የሆነን ትትናም ተላብሶ ከቅድስድንግል ተወለደ
ኦ! እናንተ የአማንያን ጉባኤ ዙሩና ኑ። ከድንግል የተወለደውን እናመስግነው። ከዘመናት በፊት ክብሩና የባርይው መልክ የሆነው እርሱ አሁን ከእኛ ጋር በድህነት/በእጦት የሚሰቃይ ሆነ ። የእግዚአብሔር እጅግ አስደናቂ ኃይና መልክ የሆነው እርሱ የባያን መልክ ያዘ ። ያ ብርሃናትን እንደ ልብስ የሚጎናጸፈው እርሱ ባዶ እንደሆነ ከሰዎች ጋር ብረት አደረገ ። ያ በኪሩቤልና እልፍ አእላፍ በሆኑት መላእክት የሚዘመርለት በምድር ላይ እንደ ዜጋ ኖረ። ያ ከሁሉም በፊት የነበረው ሁሉንም ያው ያደረገው የመጀመሪያውን ሰው ያው ያደርግ ዘንድ ከቅድስድንግል ተወለደ
ክርስቶስ አምላካችን ከእግዚአብሔር አብ የሆነውን መጀመሪያ የሌለውን ይወት ተካፋይ ሆኖ ሳለ መጀመሪያ ወደ ሌው መለኮታዊ መጀመሪያ ከፍ ያደርገው ዘንድ መጀመሪያ ያለውን የሰው ይወት ነ
 
ከድንግል ማርያም የባያን መልክ ነ። የሰማያዊው መልክ ተካፋዮች ያደርገን ዘንድ እርሱ ከአፈር የተራውን አካል ተዋሐደ አባቱ ቀኝ በብረት እንቀመጥ ዘንድ እርሱ በቅድስት ድንግል እግሮች ላይ ተቀመጠ ። የዘላለማዊ ይወት ወራሾች አድርጎ ይገልጠን ዘንድ የተዋረደን አካል ተዋሐደ በዚህም በማፀን አደረ ። በኃጢአት ምክንያት ጠፍቶ የነበረውን አዳም ያድሰው ዘንድ የማይወሰነው እርሱ በቅድስት ድንግል ማፀን ተወሰነ።
የአብ ኃይሉ ፣ ሕያውምንጭ የሆነው ክርስቶስ አምላካችን በእርሱ ያው በሆነው ድምፅ ላመኑት ሕይወትን መልቶ የያዘ ምጢር ነው ። በእርሱ ተስፋ ሚያደርጉት ላይ ፍጻሜ የሌለውን ሕይወት በነየሚሰጥ በመንፈስ ቅዱስ ጸጋም የሚያበራላቸው እርሱ ነው ። በእምነት (ሆነው) የተጠሙ ያው፣ ዘወትር ከሚፈሰው ጣፋጭም ሆነው ዚህ ምንጭ ይመላሉ ፣ ይረካሉም
እርሱ ወጣትና ሽማግሌዎች ፣ ለፃናትና ለሴቶች የድኅነታቸው አጋዥና ምንጭ ስለሆነ በዚህ ምክንያት በአንድ ድምሆነን ሥግው ቃልን እናመስግን። ከቃላት በላይ የሆነው መለኮት ምንጭ ከድንግል ማርያም ጸጋንና ነጻ የሆነውን የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ አፈለቀ ። በኃጢአት ምክንያት ሙቶ የነበረውን ያው ያደርግ ዘንድ ከአንዷ ቅድስት ድንግል እጅግ ውድ የሆነው ሉል ወጣ/ተወለደ
እርሱ በምድር ላይ የበራ የጽድቅ ፀይ ነው። በሰው መልክ ከእኛ እንዳንዱ ለመሆን ራሱን ዝቅ አደረገ። የመለኮታዊውን ክብር ነፀብራቅ በሰውነቱ ሰውሮ እኛንም በመለኮታዊው በመንፈስ ቅዱስ ሞልቶ አምላካዊ የሆነውን የምስጋና መዝሙር እንድንዘምር የተገባን አደረገን
ይቀጥላል


[1]ይህ አገላለጽ (ከብርሃን የተገኘ ብርሃን) ዘመን የማይሰፈርለት ወይም ዘመን አያም ጊዜ የሚባለው መለኪያ ከመፈጠሩ በፊትና ከጊዜ ውጪ የሆነ መለኮታዊ ምጢር እንደሆነ ለማመላከት ነ
[2] “ጣፋጭ የሆኑ ትምህርቶች” የሚለው ከስህተት ከኑፋቄ የጸዱ ትምህርቶች የሚለውን የሚያመላክት ነው። እዚህ ዓረፍተ ነገር ላይ “ትምህርትን” እንደ ምስጋና ማቅረቢያ መንገድ ተጠቅሞበታል
[3]ዙሩ ከኃጢአት ከቀደመ አኗኗር ከክህደት መመለስን ያመላክት ይችላል።
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ
አዳዲስ መጻሕፍትን ይግዙ

ተዛማጅ ጽሑፎች

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ