የትምህርቱ ርዕስ | በቃልህ ይባረኩ

“አቤቱ ቃልህ በሰማይ ለዘላለም ይኖራል” መዝ. 118፡89 ።

ቃል ያለህ እግዚአብሔር ሆይ ፣ ወዳጅነትህ ብርቱ ነው ። ወዳጅ ለወዳጁ ቃል አለው ። ቃል የልብ መልእክተኛ ነው ። ልብህን ያየንበት ቃልህ ቡሩክ ነው ። ራሳችንን ያገኘንበት ቃልህ ድንቅ ነው ። ለቃላችን ቃል ስትሆነው አፈ ማር እንባላለን ። ቃላችንን ቃልህ ሲቃኘው ከአንደበት ዳኅፅ እንተርፋለን ። አቤቱ ቃልህ በምድር ላይ ክብር ባያገኝ ቃልህ በሰማይ ለዘላለም ይኖራል ። ቃልህን መስማት የሚናፍቁ ቅዱሳን መላእክት በርግጥ አሉ ። ቃላችን በሚያዝበት ምድር ላይ ሁከት በዝቷል ፣ ቃልህ በጸናበት ሰማይ ግን ሰላም ጸንቷል ። በምድር ላይ ለሁልጊዜው አንቆይም ፣ በሰማይ ግን በዘላለማዊ ቃልህ እየጸናን ለዘላለም እንኖራለን ።

የካብነውን ስንንድ ፣ የሾምነውን ስናወርድ ፣ ቋሚ ወዳጅ ቋሚ ጠላት የለም ስንል ቃላችን በምድር ላይ ለዕለት አይቆይም ። ፖለቲካን ስንኖረው ፣ ኑሮን ፖለቲካ ስናደርገው በገዛ ቃላችን ደክመናል ። ቃልህ አገር አለው ። ቃልህ የቅዱሳን ምግብ ነው ። ቃልህ ነዋሪና የሚያኖር ነው ። ቃልህ የጊዜ ድንበርን የሚሻገር ነው ። በክንፍህ መዘርጋት ከጥፋት ቀን የጋረድከን አማኑኤል ሆይ ፣ ቃልህ ይድረሰን ! ሰማይን ያለ ባላ ፣ ምድርን ያለ ካስማ ያቆመ ቃልህ ያጽናን ! ሰማይን ከነግሡ ምድርን ከነልብሱ የፈጠረ ቃልህ እንደገና ይሥራን ። የልጅ ልጆቻችን በቃልህ ይባረኩ ። አሜን !

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
መጋቢት 15 ቀን 2015 ዓ.ም.

በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም