መግቢያ » ግጥም » በእገሌ ቤት ውስጥ

የትምህርቱ ርዕስ | በእገሌ ቤት ውስጥ

እገሌ

                                        ቤተ ጳውሎስ፤ ሐሙስ፣ ሚያዚያ 4 2004 ዓ.ም.
የሲናን በረሀ የቃዴስ
በእሳትና መብረቅ በማረስ
እልፍ ነፍሳትን በቁጣ አቅልጦ
ምርጡን ለራሱ አብልጦ መርጦ
በእንቅጥቅጥ ፍርሀት               
በህግ ስርዓት
ልብን እያራደ
ብርቱን እየናደ

ያ የብሉይ መስዋዕት

የጊዜው ፍትሀት
በአንድ ማንነቱ በውል ባልታወቀ
(እ)ገሌ በተባለ
ያ አስፈሪው ሥርዓት በድንገት አለፈ፡፡
        ለኃጢአተኞች እረፍት
        መጽናናትና ህይወት
        አንዴ ተሰውቶ የዘለዓለም ፈውስ
        መንፃትና ስርየት ፍጹሙን መቀደስ
        በእምነት ህይወትን ዘወትር እያደለ
        በምሴተ-ሀሙስ በእገሌ ቤት ውስጥ የኪዳኑ መስዋዕት እንዲህ ተቋቋመ።
ትንሹን አክባሪ
ያልታወቀን ጠሪ
በምሴተ-ሀሙስ ድግሱን ደግሶ
ፍጥረትን ጋበዘ ሥጋ ደሙን ቆርሶ፡፡
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም