መግቢያ » ግጥም » ተመስገን ጌታዬ

የትምህርቱ ርዕስ | ተመስገን ጌታዬ

ጸጋህ አይጓደል ተመስገን ጌታዬ ፣
ሁሉን ያረክልኝ ባለውለታዬ ፤
አንድ አለኝ የምልህ ዘወትር ሁልጊዜ ፣
አንተ ነህ ጋሻዬ ደጋፊ ምርኵዜ ።
አቤቱ አምላክ ሆይ የሰማይ አባቴ ፣
አካሌ ሲደክም አንተ ነህ ጉልበቴ ፤
በሰላም በጤና ስኖር በዕድሜ ጸጋ ፣
ምስጋና ብቻ ነው የምሰጥህ ዋጋ ።

የኑሮዬ ባላ የሕይወቴ ቤዛ ፣
ለእኔ ያረክልኝ ውለታህ የበዛ ፤
ተመስገን ፈጣሪ ልበልህ ጠዋት ማታ ፣
ረዳቴ አንተ ነህ የቸገረኝ ለታ ።
ሲርበኝ አጉርሰህ ስታረዝ አልብሰህ ፣
ስጨነቅ አጽናንተህ ስታመም ፈውሰህ ፣
ድረስልኝ ስልህ ስምህን ጠርቼ ፣
የምፈልገውን አላውቅም አጥቼ ።

ቸኩለህ እንደ ሰው ቅጣት የማትሰጠው ፣
ሀብታምና ድሀ የማታስበልጠው ፤
ቸሩ መድኃኔ ዓለም ይድረስህ ምስጋና ፣
ረዳቴ አንተ ነህ በስምህ ልጽናና ።
ለኮንትራት ሕይወት ነገ ለሚቀረው ፣
በመንፈስ አጽናኝ ቃልህን እንዳልሽረው ፤
ኃጢአቴን ሰርዘህ አድነኝ ከዕዳ ፣
መሐሪው አንተ ነህ ለሰው ልጆች ፍዳ ።

እመካብሃለሁ በሰማዩ አባቴ ፣
የፈጠርከኝ አምላክ አውጣኝ ከኃጢአቴ ፤
ሳዝን ፈጥነህ ደራሽ ስከፋ መካሪ ፣
መከታ ጋሻዬ አንተ ነህ ፈጣሪ ፤
ዕዝራ በመሰንቆ ዳዊት በበገና ፣
እንዳቀረቡልህ ለሥራህ ምስጋና ፣
አወድስሃለሁ እኔም በዜማዬ ፣
አንተ ነህ ጠባቂ የሕይወት ጋሻዬ ።

(ምንጭ፡- ዘለሰኛ)

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሚያዝያ 10 ቀን 2016 ዓ.ም.

በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም