የትምህርቱ ርዕስ | ትምክሕቴ አንተ ነህ

 “የሚመካ በእግዚአብሔር ይመካ ተብሎ እንደ ተጻፈው ይሆን ዘንድ፥ ከእግዚአብሔር ዘንድ ጥበብና ጽድቅ ቅድስናም ቤዛነትም በተደረገልን በክርስቶስ ኢየሱስ የሆናችሁ ከእርሱ ነው ።” 1ቆሮ. 1፡30-31
በጥበቤ እንዳልመካ ጥበቤ ይዘነጋኛል ፣ በጉልበቴ እንዳልመካ ጉልበቴ ይከዳኛል ፣ በሀብቴ እንዳልመካ ሀብቴ እንደ በረዶ ይሟሟል ፣ በዝናዬ እንዳልመካ ተረኛ ዝነኛ ይነጥቀኛል ፣ በኃይሌ እንዳልመካ ኃይሌ ይዝልብኛል ፣ በሰራዊት እንዳልመካ ይበተንብኛል ፣ በውበቴ እንዳልመካ ውበቴ ይበላሽብኛል ፣ በፍቅሬ እንዳልመካ ፍቅሬ በጥላቻ ይለወጣል ፣ በአገልግሎቴ እንዳልመካ የገነባሁትን ላፈርሰው እችላለሁ ፣ በወዳጅ እንዳልመካ ከስፍራው አጣዋለሁ ፣ በትላንት እንዳልመካ አልፎ ተረት ይሆንብኛል ፣ በዛሬ እንዳልመካ ባሰብሁበት መዋል ያቅተኛል ፣ በነገ እንዳልመካ ቀን የሚያመጣውን ማወቅ ያቅተኛል ፣ በቅድስናዬ እንዳልመካ አንዱን ስደፍን አንዱ ያፈስብኛል ።
የምመካበት ያሳፈረኝን ፣ የምመካበትን የፈራሁትን ፣ የምመካበት ያጣሁትን እኔን ልጅህን ትምክሕት ልትሆነኝ ሰው የሆንህ ፣ በቀራንዮ የዋልህ የእግዚአብሔር ልጅ ሆይ ተመስገን ። ጽድቅ ለሌለኝ ጽድቅ ፣ ቅድስና ለሌለኝ ቅድስና ፣ ጥበብ ለሌለኝ ጥበብ የሆንከኝ አንተ ነህ ። ቤዛ ማቅረብ ለማልችል ቤዛ የሆንከኝ ፣ ከሞትም ያዳንከኝ የእግዚአብሔር ልጅ ሆይ ምስጋናዬ ይድረስህ ። ከሚያባርረኝ ጠላት ፣ ከሚያሳድድ ሕሊና የተማጸንሁብህ የደኅንነቴ ቀንድ አንተ ነህ ። የማትደፈር ምሽግ ሁነህ ከሁሉ የምታድነኝ አንተ ነህ ። የዘራሁት ሲመክን ፍሬን የምትሰጠኝ ፣ የሠራሁት ሲፈርስ አዲስ ገንብተህ የምታኖረኝ አንተ ነህ ።
አንተ ትምክሕቴ ነህ ። የደኅንነቴም ራስ ነህ ። ለሚያልፈው ዓለም ብቻ ሳይሆን ለማያልፈው ዓለምም እሻሃለሁ ። አንተ ካላቅኸኝ የሚያሳንሰኝ ፣ አንተ ከወደድከኝ ከንቱ የሚለኝ ማንም የለም ። ቢኖርም ሐሰተኛ ነው ። ዛሬን ያየሁብህ ትምክሕቴ ተመስገን ። በማይፈጸም ዘመን ለዘላለሙ አሜን ። የሚሰማ ሁሉ በልቡ ያክብርህ ፣ በአንደበቱ ይዘምርልህ ፣ በጉልበቱ ይስገድልህ ።
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም