የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ

የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ 

ኃጢአት ያንቺ ዕድሜ

                                                                                        ማክሰኞ፣ ጥቅምት 14 2004
አይዘከር ግብርሽ
አይታወስ ስምሽ
ውሃ እያራሰ እንዲያው ያለቅልቅሽ
አይቁምልሽ ሐውልት መታሰቢያ ቅጥር
 አፀድሽ ይነቀል
          መሠዊያሽ ይቃጠል
አያጣፍጥ ጨውሽ
           አያስማ ሙቀትሽ፡፡
መሠረትሽ ይናድ የቤትሽ ምሰሶ
እኔ ግን ልነሣ በንስሐ ልቅሶ
የቆረጥኩት መልካም ይለምልም አብዝቶ
እንደ ወይን ፍሬ ተውቦ ጎምርቶ
ልቁም ሙሉ ሆኜ በልቤ ታድሼ
በማይጥለኝ ጌታ በጸጋው ጎልምሼ
ያንቺ ቤት ግን ዳግም:-
በጅማሬ ይቁም አያግኝ ፍጻሜ
ቀጥ ይበል አይርዘም
ኃጢአት ያንቺ ዕድሜ
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ
አዳዲስ መጻሕፍትን ይግዙ

ተዛማጅ ጽሑፎች

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ