ማክሰኞ፣ ጥቅምት 14 2004
አይዘከር ግብርሽ
አይታወስ ስምሽ
ውሃ እያራሰ እንዲያው ያለቅልቅሽ
አይቁምልሽ ሐውልት መታሰቢያ ቅጥር
አፀድሽ ይነቀል
አያስማ ሙቀትሽ፡፡
መሠረትሽ ይናድ የቤትሽ ምሰሶ
እኔ ግን ልነሣ በንስሐ ልቅሶ
የቆረጥኩት መልካም ይለምልም አብዝቶ
እንደ ወይን ፍሬ ተውቦ ጎምርቶ
ልቁም ሙሉ ሆኜ በልቤ ታድሼ
በማይጥለኝ ጌታ በጸጋው ጎልምሼ
ያንቺ ቤት ግን ዳግም:-
በጅማሬ ይቁም አያግኝ ፍጻሜ
ቀጥ ይበል አይርዘም
ኃጢአት ያንቺ ዕድሜ