መግቢያ » ግጥም » አስበን

የትምህርቱ ርዕስ | አስበን

በጸናው የምስጋና ርስትህ ፣

በማይደፈረው ግዛትህ ፣

በማይናወጸው ዙፋንህ ፣

በማይለያየው አንድነትህ ፣

በማይጠቀለለው ሦስትነትህ ፣

በማይሰጋው መንግሥትህ ፣

በማይታበለው ቃልህ ፣

በማያማክሩት ጥበብህ ፣

በማይመረመር ማስተዋልህ ፣

በማያበድሩት እውቀትህ ፣

በማይፈርስ ምክርህ ፣

በማይክደው አባትነትህ ፣

በማይቀየመው አፍቃሪነትህ ፣

በማይሰለቸው ቸርነትህ ፣

በማይገፋው ጥላህ ፣

በማያባርረው ማደሪያህ ፣

በማይዘናጋው ጥበቃህ ፣

በማይጠገበው ጣዕምህ ፣

በማይሻረው ፍርድህ ፣

በማይጨክነው ርኅራኄህ ፣

በማይጥለው ትዕግሥትህ ፣

በማይካደው ጻድቅነትህ ፣

በማያልፈው ስጦታህ ፣

በማይነጥፈው እጅህ ፣

በማይዝለው ትከሻህ ፣

በማያባራው ምስጋናህ ፣

በማይተካው ጌትነትህ ፣

በማይሰረቀው አምልኮህ ፣

በማይሞተው ሕያውነትህ ፣

በማይገሠሥ ሥልጣንህ ፣

በማያልፍ ዓይንህ ፣

በማያፈስስ ጆሮህ ፣

በማይሰበር ምክርህ ፣

በማይነገር ሐሤትህ ፣

በማይሸነፍ መድኃኒትህ ፣

በማይደመሰስ መሐላህ ፣

በማይቀር ኪዳንህ ፣

በማይከዳ ወዳጅነትህ ፣

በማይረሳ ወንድምነትህ ፣

በማያጋልጥ እናትነትህ ፣

በማይታዘብ አበ ነፍስነትህ

አቤቱ አሁን አስበን !!!
የነግህ ምስጋና /15
መጋቢት 12 ቀን 2012 ዓ.ም.
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም