የትምህርቱ ርዕስ | አደገኛ ነው

ኃጢአት የመንገድ እንቅፋት ሊሆን ይችላል ፣ የሕይወት ግብ ከሆነ አደገኛ ነው ፡፡ ቁሳቁስ ስኬት ሊሆን ይችላል ፣ ሕይወት ከሆነ አደገኛ ነው ፡፡ ወዳጆች የሚያስደስቱ ሊሆኑ ይችላሉ ፣ እግዚአብሔርን የሚተኩ ከሆኑ ግን አደገኛ ነው ፡፡ በሥራ መትጋት መልካም ነው ፣ ቤተሰብን መበተን ግን አደገኛ ነው ፡፡ ትምህርት አስፈላጊ ነው ፣ ሳይማር ያስተማረን ወገን የምንንቅበት ከሆነ ግን አደገኛ ነው ፡፡ በሰው አገር መኖር ምቾት ሊኖረው ይችላል ፣ የወገንን ፍቅር በምቾት መለወጥ ግን አደገኛ ነው ፡፡ ፖለቲከኞችን መቃወም ጊዜው የፈቀደው ሊሆን ይችላል ፣ አገርን መጥላት ግን አደገኛ ነው፡፡ ከዝሙት ለመራቅ ከተቃራኒ ጾታ ጋር በገደብ መኖር መልካም ነው ፣ ተቃራኒ ጾታን መጥላት ግን ተገቢ አይደለም ፡፡ ገንዘብ ለማግኘት መትጋት ተገቢ ሊሆን ይችላል ፣ ያለ ገንዘብ አልኖርም ብሎ ማሰብ ግን አደገኛ ነው ፡፡ ኑሮን በሥርዓት መምራት ተገቢ ነው ፣ ቤተሰብን እያስራቡ ገንዘብ ማጠራቀም ግን አደገኛ ነው ፡፡ ሰውን ማስደሰት መልካም ነው ፣ ሰውን ሁሉ ማስደሰት ግን አደገኛ ነው ፡፡ 

ንግግር መቻል ጸጋ ነው ፣ ተናጋሪ ብቻ መሆን ግን አደገኛ ነው ፡፡ እውነትን መያዝ የማይገኝ ዕድል ነው ፣ ሌላውን መቃወም ግን አደገኛ ነው ፡፡ ማፍቀር መልካም ነው ፣ ማምለክ ግን አደገኛ ነው ፡፡ ተስፋ መስጠት መልካም ነው ፣ መልሶ መቆጨትና ማዘግየት ግን አደገኛ ነው ፡፡ ትዳር መልካም ነው ፣ መውረጃ ፌርማታ መፈለግ ግን አደገኛ ነው ፡፡ ምንኩስና ዘመንን ለእግዚአብሔር መስጠት ነው ፣ ከነቆብ መዝለል ግን አደገኛ ነው ፡፡ አንድን ነገር ከልብ መያዝ መልካም ነው ፣ ከእርሱ ውጭ ሌላ ማሰብ አለመቻል ግን አደገኛ ነው ፡፡ ራስን መካድ ክርስትና ነው ፣ ራስን መጣል ግን አደገኛ ነው ፡፡ ሰውን ማዳመጥና ማማከር መልካም ነው ፣ የሰውን ምሥጢር መሰርሰር ግን አደገኛ ነው ፡፡ አለመበደል መልካም ነው ፣ ካፈርኩ አይመልሰኝ ማለት ግን አደገኛ ነው ፡፡
የደስታ ቋጠሮ/11
ተጻፈ አዲስ አበባ
ሐምሌ 5/2010 ዓ.ም.
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን  
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም