የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ

የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ 

ኢየሱስ ናዝራዊ

ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአብሮ አደጎቹና ዘመዶቹ ተራ ሕልም ያለው ተደርጎ ይታያል ። ፖለቲከኞች ለወንበራቸው የሚያሰጋ የዙፋን አደጋ አድርገው ቆጥረውታል ። የሃይማኖት አባቶችም በትክክል አገልግለው የሚያገኙትን እንጀራ በግብዝነት ተውኔት ከሕዝቡ ለማግኘት ፈልገዋል ፣ በዚህም ኢየሱስን የጥቅማቸው ተጋፊ ብለው በመፈረጅ ከቅናታቸው ጥልቀት የተነሣ ለሞት ከጅለውታል ። ደቀ መዛሙርቱም የተጨቆነ ኑሮ መኖር ሰልችቷቸው ነበርና የዳዊትን መንግሥት አስመላሽ አድርገው ገምተውታል ። ባለጠጎችም የሀብት ተቀናቃኝና የምቾት እንቅፋት ብለው ሰይመውታል ። ማኅበረሰቡም ሰው የማይመርጥ ዘማዊና ቀራጭ ወዳድ አድርጎ ሥሎታል ። ኢየሱስ ጌታችን ለብዙዎች ጥያቄ ላመኑበት ግን መልስ ነው ።

በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ
አዳዲስ መጻሕፍትን ይግዙ

ተዛማጅ ጽሑፎች

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ