መግቢያ » ልዩ ልዩ ሁለት » እስክመጣ

የትምህርቱ ርዕስ | እስክመጣ

በመጀመሪያ የምታውቀኝ ፣ መጀመሪያን የሰጠኸኝ ፣ አባት እናቴ ሳያዩኝ ከዓለም በፊት ያየኸኝ ፣ ወዳጆች ከማይከተሉበት ከመቃብር በኋላ ዘመድ የምትሆነኝ ፣ ለቀንህ ምሽት ፣ ለብርሃንህ ጽልመት የሌለብህ ፣ ድሀውን እንዲሁ የምታስደስት ፣ ያለ ድጋፍ ሰማይን ያቆምህ ፣ የምስኪኗን ማድጋ በዘይት የሞላህ የፍቅር አባት እግዚአብሔር ሆይ አመሰግንሃለሁ ። “ሰላም ለእናንተ ይሁን” የምትለው በመምጣትህ ሞት ፣ በመናገርህ ሁከት የሚበረግግልህ ፣ ለሕይወቴ ሕይወት ፣ ለአገሬ ሰላም ትሰጥ ዘንድ እለምንሃለሁ ። እንዳልተቃኘ በገና ፣ እንዳልተጠገነ ማጫወቻ ድምፄ የሚረብሸውን ፣ ምሬትን እንጂ ምስጋናን ማመንጨት ያልቻልሁትን ቃኝተህ የክብርህን ዜማ ስጠኝ ። ከባለጠጋው ግብዣ ፣ ከንጉሡ ገበታ ድሀ አይገኝም ። ነዌን በገንዘቡ ያላፈርኸው ፣ አልዓዛርን በቍስሉ ሳትጠየፍ በቤትህ የጋበዝኸው ፣ እኔንም ከታላቁ እራት አትለየኝ ። ሰዎች ሲቆጥሩ የገደፉኝን ፣ ከቍጥር የማልገባውን ፣ ከሰው ተራ የማልመደበውን አንተ የአብ ልጅ ተቀበለኝ ። ብዙ አባክኜ የመጣሁ ፣ በረከቴን ፣ ጤናዬን ፣ ሰላሜን በመናኛ ቦታ የጣልሁ ነኝና መንፈስ ቅዱስ ሆይ ናዝዘኝ ። ዞሬ ስመጣ የማገኝህ ፣ ልቤን ስዘጋብህ በርህን ከፍተህ የምትጠብቀኝ ፣ ካደረሱብኝ በላይ የደረስክልኝ አንተ አምላኬ ነህና አመሰግንሃለሁ ። እየቻልሁ ያላደረግሁትን ፣ እያልቻልሁ ላደርገው እመኛለሁ ። ባለፈው ዕድሌ ሳይሆን ባለው ዕድሌ መጠቀምን ስጠኝ ። ጸጸት ንጉሥ ሁኖ አይግዛኝ ። ውዳሴ ለተወደስከው ይሁንልኝ ። እስከመጣ ሰላም እልሃለሁ ። አሜን ።

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ታኅሣሥ 18 ቀን 2014 ዓ.ም.

በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም