መግቢያ » ግጥም » ኪዳን አለኝ እኔ

የትምህርቱ ርዕስ | ኪዳን አለኝ እኔ

              ሰኞ ታኅሣሥ 9 2004
ንፋሱን ቀስቅሰው
ሞገዱን አናውጠው
ቀስትህን ገትረው
ሰይፍህን ሰይፈው
አሹለው ጥርስህን
ከስክሰው ፊትህን
ግንባርህን ቋጥረው
ቁጣህን ተቆጣው

ጩኸትህን ጩኸው
ጭፍራህን ቀስቅሰው
ወድረው ጦርህን
ዘርጋው ወጥመድህን
ጉድጓዱንም አስፋው
ጅራፍህን ግመደው
የቤቴን ምሰሶ አብዝተህ ነቅንቀው
ከፊቴ ያለውን ሁሉንም ውሰደው
እንዲህ ተግዳሮትህ ገንፍሎ ሲወጣ
ብዙ ይጠቅመኛል በነፍሴ ልሠራ
ይደንቀኛል ክንዱ የጌታ ፈቃዱ
ሰልፉን ለእጆቼ ሲያሳይ በጥበቡ
ካንተ ሺህ ተግዳሮት ብዙ ዘመን ቀድሞ
ኪዳን አለኝ እኔ
ንፋስህ ላይነቅለው ጎርፍህም ላይነካው የእኔን ቤት ፈጽሞ
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም