1- ከሰው ጋር ንግግር ከመጀመርህ በፊት በማለዳ ጸልይ ።
2- አእምሮህን ሰፊ ለማድረግ ቀኑን በንባብ ጀምር ።
3- ከእንቅልፍ እንደ ተነሣህ የዓለምን ወሬ አትስማ ።
4- ያላለቀው ጉዳይህ የዛሬው ሥራህ ነውና ተደሰትበት ።
5- ንጽሕናህን ጠብቅ ፣ ለራስህ ያለህ ክብር ማሳያ ነውና ።
6- ሁሉም ነገር ከተሳካ የምትሠራው አይኖርህምና ሁሉም ነገር ይሳካ ከማለት ተቆጠብ ።
7- ለትምህርት የዕድሜ ገደብ የለውምና እስክትሞት ተማር ።
8- ለሚወዱህና ለሚያከብሩህ ቅድሚያ ስጥ ።
9- ጉዳይን ከባለቤቱ እንጂ ከሦስተኛ ሰው አትስማ ።
10- በትሕትና ለሚያገለግልህ ክብር ይኑርህ ፣ ምቹ ነገርንም አዘጋጅለት ።
11- ባዶ እጅህን ተወልደሃልና ፣ ባዶ እጅህንም ትሄዳለህና ስለ ንብረት ሕይወትህን በብስጭት አትጉዳ ።
12- መታዘብህ ውስጥህን እንዳይጎዳው ከብልጦች ጋር ጊዜ አታጥፋ ።