መግቢያ » ልዩ ልዩ ሁለት » የማትቀየም አንተ ብቻ

የትምህርቱ ርዕስ | የማትቀየም አንተ ብቻ

እግዚአብሔር ሆይ ብርሃናት ብርሃንነትህን ፣ ፍቅሮች ፍቅርህን ፣ ቸርነቶች ቸርነትህን አያህሉትም ። ባለ መጥፋት የምትኖር ፣ ባለ መታጣት የምትገዛ ፣ ባለ መናወጥ የምትገኝ ፣ ባለ መሰሰት የምትሰጥ ፣ ባለ ማበደር ጸጋን የምትቸር ፣ ያለ ግዴታ የምትወድ አንተ ነህ ። እኔማ የጨበጥሁትን ስለቀው ፣ የለቀቅሁትን ስይዘው ፤ ያወደስሁትን ሳራክሰው ፣ የረገምሁትን ስቀድሰው ፤ የሸኘሁትን ሳሳድደው ፣ አሳድጄ የያዝሁትን ስሰለቸው ፤ ያቀፍሁትን ስገፈትረው ፣ የገፈተርሁትን ሳቅፈው ፤ አበባ የሰጠሁትን አፈር ስበትንበት ፣ ትቢያ የረጨሁትን ወርቅ ሳለብሰው የምኖር ፣ እኔ እኔን መልመድ ያቃተኝ ፍጡርህ ነኝ ። እኔ እኔን ሳላውቀው ለብዙ ዘመን እኖራለሁ ። እኔ አንተን ብሆን ኖሮ እኔን አልፈጥረውም ነበር ። እኔን እኔ ስጠላው አንተ ግን እኔን ወደድኸው ። በነፋሱ አቅጣጫ እንደ ባንዲራ እውለበለባለሁ ። ይሙት ሲባል ከሰማሁ ይገደል እላለሁ ። አቋምና አቋቋም ያጣሁትን ልጅህን በመልካም አስበኝ ። ኖሬ ካልሞትሁ ሞቼ እኖራለሁና እባክህ አግዘኝ ። ማደሪያ ቤቴ ፣ መተዳደሪያ ቀለቤ አንተ ነህ ። ያለፈውን በረከት አድፋፍቼ ዛሬም ስለምንህ ሂሳብ እንተሳሰብ ሳትል ትሰጠኛለህ ። የማትቀየም አንተ ብቻ !

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ታኅሣሥ 10 ቀን 2014 ዓ.ም.

በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም