የትምህርቱ ርዕስ | ያማረ ይሁን !

“አቤቱ ፥ ረድኤቴ መድኃኒቴም ፥ የአፌ ቃልና የልቤ አሳብ በፊትህ ያማረ ይሁን ።” መዝ. 18 ፡ 14 ።

ጌታ ስለሆንህ ጌታ የምንልህ ፣ አምላክ ስለሆንህ አምላካችን ያልንህ ፣ ንጉሥ ስለሆንህ ንጉሣችን ብለን ያነገሥንህ ፤ ለጥበብህ መመርመር ፣ ለባሕርይ ሞት ፣ ለብልጥግናህ እጦት ፣ ለኃይልህ መድከም ፣ ለህልውናህ መታጣት ፣ ለመቅረብህ መራቅ ፣ ለርቀትህ መደረስ የማይስማማህ ፣ እኔ ብለህ ለመናገር አንተ የሆንከው ፣ ለጠባይህ ለውጥ የሌለብህ ፣ ሰው ወዳጅ እግዚአብሔር ሆይ አቤቱ አቤቱ እንልሃለን ። ከርግብ አንሰን በአንድ ቃል ኪዳን መጽናት ቢያቅተን ፣ ከውሻ አንሰን ታማኝነት ቢጎድልብን አቤት አቤት እንልሃለን ። ታላላቆች የታሪክ አቧራ ሲጫናቸው ፣ ጠቢባን የዘመን ትቢያ ሲከድናቸው የማትደብስና የማትደበዝዝ ወርቅ ኢየሱስ ሆይ እናደንቅሃለን ።

ሰዎች እንዲሆንላቸው አንፈልግም ፣ እንዲሆንልን ግን እንከጅላለን ። የልባችን አሳብ ክፉ ነውና እባክህ አሰማምረን ። የጣለው በረዶ ፣ የወረደው መብረቅ ምሬተኛ ቢያደርገን አፈ ማር ክርስቶስ ሆይ ፣ አንደበታችንን አጣፍጥልን ። የምንችለውን ማድረግ ተስኖን የማንችለውን ለማድረግ እንመኛለን ፣ ባለ ቃልኪዳኑ አማኑኤል ሆይ ለጽድቅ ቀጠሮ ከማብዛት እባክህ አድነን ። ከወፎች ዝማሬ ጋር የማለዳ ምስጋናችንን አስማማልን ። ስታነጋልንና ስታኖረን ያልከበደህ አንተ ሆይ ለማመስገን ከብዶናልና እባክህ ይቅር በለን ። ይህች ቀን ምሕረትህን ለሚጠባበቁ ዕለተ ብርሃን ትሁን ። ብዙዎች በተሳፈሩበት ስምህ ለዘላለሙ አሜን !

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
መጋቢት 18 ቀን 2015 ዓ.ም.

በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም