የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ

የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ 

ለእኔው እንዳይቀርብኝ

እግዚአብሔር ሆይ የሰዎች ምስጋና ቢቆም ሁለት ቃል የማያወሩት የመላእክት ምስጋና አይቀርብህም ። የመላእክት ምስጋና ቢቀር ምስጋናህ አይጎልብህም ። ሰዎች ሳይፈጠሩ መላእክት ያመሰግኑህ ነበር ፤ መላእክት ሳይፈጠሩ ባሕርይህ ባሕርይህን ያደንቀው ነበር ። ከምስጋና ብቆም ከደስታ የምቆመው ፣ ከቅዳሴው ብወጣ ለእኔው የሚቀርብኝ እኔው ብቻ ነኝ ። ምስጋናህ ለእኔ ክብርን ይጨምርልኛል እንጂ አንተን ከሆንኸው በላይ ከፍ አያደርግህም ። ፍጹም ነህና መሙላትና መጉደል የለብህም ። ባመሰግንህ አይሞላልህም ፣ ባጉረመርም አይጎልብህም ። ለእኔው እንዳይቀርብኝ ጌታዬ እግዚአብሔር ሆይ ተመስገን ። አሜን ።
የነግህ ምስጋና /1/

የካቲት 13 ቀን 2012 ዓ.ም.

ዲያቆን አሸናፊ መኮንን

በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ
አዳዲስ መጻሕፍትን ይግዙ

ተዛማጅ ጽሑፎች

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ