መግቢያ » ልዩ ልዩ አንድ » ለይኩን ለይኩን

የትምህርቱ ርዕስ | ለይኩን ለይኩን

 ድንጋይ ሳትወቅር ዓለማትን የሠራህ ፣ ወርቅ ሳታቀልጥ ሁሉን ያስጌጥህ ፣ አጋዥ ሳትሻ ሁሉን የፈጸምህ ፣ አማካሪ ሳትፈልግ ሁሉን በጥበብ ያከናወንህ እግዚአብሔር ሆይ ላሠራርህ እንከን ፣ ለግዛትህ ወሰን የለብህምና አንተን እናመሰግናለን ። ፊተኞች አሉኝ ብለህ የኋለኞችን የማትንቅ ፣ አርፍደው መጡ ብለህ በርህን የማትቆልፍ ፣ በጎነታቸው አነሰ ብለህ ገሸሽ የማትል ፣ ኃጢአታቸው በዛ ብለህ የማትጠየፍ የጎስቋሎች ወዳጅ ነህና ምስጋና ይገባሃል ። ከራሱ ለሚሸሸው መጠጊያ ፣ በወኅኒ ላለው በር ከፍተህ የምታወጣ ፣ በስደት ያለውን ለአገሩ የምታበቃ ፣ እናቱ የጨከነችበትን ራርተህ የምታፈቅር አንተ ነህ ። ወዴት ልሂድ ? ለሚል መድረሻው ፣ ምን ልሥራ ? ለሚል ብልሃቱ ፣ ማን አለኝ ? ለሚል አለኝታው አንተ ነህ ። ፍቅሩን ለሚያመልከው ሰው ፍቅሩን የሚያስንቅ ፍቅር ታሳየዋለህ ። ልቡ ደንዳና የሆነውን በመውደድህ ታቀልጠዋለህ ። በእውነት እኛን የተቀበለች እጅህ ትባረክ ።
እንኳን መከራ ብሥራትም የሚያስደነግጠን ደካማ ልጆችህ ነንና አቤቱ ለእኛ ራራ ። ትላንት የተሸከመችን እጅህ ዛሬም ያለ መዛል ትሸከመን ። ዝቅተኞች ብንሆንም ልዑልነትህ ከፍ ያድርገን ። በአስተሳስብ ብንወድቅም በዘላለም ምክርህ አክብረን ። የያዝነውን እየለቀቅን ፣ የለቀቅነውን ብንፈልግም የሚሻለውን ምረጥልን ። ወጥተን ለመግባት ድፍረት ቢያጥረንም በዓይኖችህ ተመልከተን ። ቢያንስብህም ምስጋናችንን ተቀበለው ። አሜን ወአሜን ፣ ለይኩን ለይኩን ፣ ይሁን ለይሁን ።
የነግህ ምስጋና /4
የካቲት 18 ቀን 2012 ዓ.ም.
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም