መግቢያ » ልዩ ልዩ ሁለት » ስላለህ አለሁ!

የትምህርቱ ርዕስ | ስላለህ አለሁ!

እኔ አለሁ ጌታዬ፣ አንተስ እንደምን አለህ? ድሆች በረከትን፣ ግፉዓን ፍርድን ፣ ብቸኞች የመኖር ጉልበትን ይለምኑሃል። ቀኑ ያደከማቸው “ልበ ሰፊ ፣ ነገር አላፊ አርገኝ” ይሉሃል። ጥሩ ኑሮ ሳይሆን ጥሩ ሞት በሚናፈቅበት ዘመን መኖር ገራሚ ነው። ካንተ ካልሆነ ይህ ከወዴት ይገኛል? ሁሉ የሚገኝብህ መዝገብ ሆይ በመኖር ስለባረከኝ ተመስገን! ስጠራጠርህ እየታመንህልኝ ፣ በጠላቶች ጉልበት ልክ ስለካህ አንተ አልተቀየምከኝም። ፈራጅ የለም ስልህ አንተ ግን በማይናወጥ ዙፋን አለህ! ምን እልህ ይሆን? የፈጠርከውን ላልፈጠረ ጨካኝ አሳልፈህ አትስጠው። ዘመኑን ብቻ ሳይሆን እኛንም ለውጠን። ልብ ለልብ መገናኘት ተረት እንዳይሆንብን አስበን። ዓመቱን በሰላም አስፈጽመን! ምስጋናችን ይኸው ይድረስህ!

በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም