የትምህርቱ ርዕስ | በበጎ ፈቃዱ

“በበጎ ፈቃዱ እንደ ወደደ ፥ በኢየሱስ ክርስቶስ ሥራ ለእርሱ ልጆች ልንሆን አስቀድሞ ወሰነን ።” ኤፌ. 1 ፡ 5 ።

ቫላንታይን ዴይ /የፍቅረኞች ቀን/ እየተባለ የሚጠራው የጣኦት አምልኮ ፣ ዘመናዊ ስያሜና ልምምድ አግኝቶ በወጣቶች ዘንድ እየተከበረ ይገኛል ። ወጣቶችም የሚያከብሩት ራሳቸውን በማዋረድ በመሆኑ በዓሉ መንፈሳዊ ክብር የሌለው ነው ። በዚህ ቀን ወጣቶች ቀይ ለብሰው ፣ ቀኑን ሲውሉ ምሽቱን ደግሞ ደማቸው ፈስሶ ፣ ድንግልናቸውን አጥተው ያድራሉ ። በቀይ ባንዲራ የዋለው ተረፈ ጣኦት ፣ ቀይ መስመር ውስጥ በማስገባት የወጣቶችን ሕይወት ይቀጫል ። በዚህ ቀን ዘላቂ ሕይወታቸው የሚበላሽባቸው ወጣቶች የትየለሌ ናቸው ። የጥንት የጣኦት አምልኮዎች ከዝሙት ጋር ጥብቅ ግንኙነት አላቸው ። ዝሙት ሥጋን ፣ ነፍስንና መንፈስን የሚያረክስ በመሆኑ የአጋንንት ትልቅ መሥዋዕት ነው ።

ወደ መንፈሳዊው ዓለም ስንመጣ የፍቅር ቀን የሚባል የለም ። ፍቅር ቀን የለውም ፣ ዘላለማዊ ነው ። ያ ፍቅርም እግዚአብሔር ነው ። መንፈሳዊው ፍቅር ቀይ በመልበስ የተገለጠ ሳይሆን ደሙን ባፈሰሰልን በክርስቶስ ሞት ላይ ያበበ ነው ። ይህ ፍቅርም ወደ ንጽሕና የሚጠራ ፣ ዝሙትን የሚረታ ነው ። ወጣቶችንም እንኳን የሚጎዳውን ኃጢአት ለመተው ይቅርና ሕይወታቸውን ለሰማዕትነት ለመስጠት የሚያስጨክን ፣ እነ ቅዱስ ጊዮርጊስን ለሰማዕትነት ያበቃ ነው ።

ባሕል የሚመስሉ ጎጂ ነገሮች ፣ በዓል የሚመስሉ ውድቀቶች ፣ ከሌላው ዓለም የተቀዱ የሚመስሉ ዘመናዊነት የተላበሱ የደፈረሱ ውኃዎች ሊታሰብባቸው ይገባል ። በዚህ በፍቅረኞች ቀን የመገናኛ ብዙኃን ሳይቀሩ አልጋ ቀረሽ ወሬ እያወሩ ፣ ስለተላላፊ በሽታዎች በሚነገርበት ዘመን ሞራልና ጤናው የወደቀ ትውልድ እያተረፉ ናቸው ። ይልቁንም ስሜት እንጂ እውቀት የሌላቸውን ወጣቶች በጭድ አጠገብ ያለ እሳት እየሆኑባቸው ያሉ ሚዲያዎች በሕግ ሊጠየቁ ፣ በሃይማኖት ሊወገዙ ይገባቸዋል ።

እኛ የምናከብረው የፍቅር ቀን የለንም ። ያከበረን ፍቅር ግን አለ ። ይህንንም ፍቅር የምናከብረው ዘወትር ለሌሎች መሥዋዕት በመሆንና በተለወጠ ሕይወት ነው ።

የእግዚአብሔር ፍቅር በጎ ፈቃድ ያለው ነው ። የዓለም ፍቅር ግን ክፉ ምርጫ ያለበት ነው ። ፍቅር እግዚአብሔር ነውና እግዚአብሔርን የሚያሳዝን ግብር ሁሉ የፍቅር ስም የተሰጠው ውድቀት ነው ።

የኤፌሶን መልእክት ትርጓሜ /8

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
የካቲት 10 ቀን 2014 ዓ.ም.

እባካችሁ ለሌሎች አካፍሉት

በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም