ከለምለም ቅጠል በላይ ደስታዬ ፣
ከሚፈልቀው ይልቅ እርካታዬ ፣
ከመንገድ በላይ መድረሻዬ ፣
የዕለት የዘለቄታ ሳይሆን የዘላለም ማረፊያዬ ፣
በመቃብሬ ላይ ይነሣል ብላህ የጻፍህ ፣
የተጠላሁትን ያፈቀርህ፣ የሰይጣን መልክ ሲሰጡኝ መሳይ ልጄ ያልከኝ ፣ የተነቀፍሁትን ያመንከኝ፣ ወርቅህን እኔ ጭቃው ላይ የጣልህ ፣ መክሊትህን ለአባካኙ የሰጠህ ፣ ጸጋህን ለተራቆተው የናኘህ …
አንተ እኮ እግዚአብሔር … ።
ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ሐምሌ 1/2016 ዓ.ም.