መግቢያ » ልዩ ልዩ ሁለት » እስከ መቼ አትምረንም ?

የትምህርቱ ርዕስ | እስከ መቼ አትምረንም ?

ጌታ ሆይ የምንጠብቀው የሚጠብቀን ካንተ በቀር ማነው ?

ቸር ሆይ! ያለንን ሁሉ እየተነጠቅን የሌለንን የምንናፍቀው ምስኪኖች ካንተ በቀር ሰጪአችን ማነው?

ወጋገን አየን ስንል የሚጨልምብን ፣ ከእህል ረሀብ ወደ ፍቅር ረሀብ የተሸጋገርን ካንተ በቀር ተስፋችን ማነው ?

ፍቅር ጌታ ሆይ ! የማልቀሻ ስፍራችን ፣ ሸክም የምናራግፍባት ደጀ ሰላማችን ፣ ደምን በይቅርታ ፣ በደልን በፍቅር የምንለውጥባት አንድ ዓይናችን የሆነች ቤተ ክርስቲያን ስትጎዳ ካንተ በቀር የሚያድናት ማነው ?

ገዳይም ሟችም እኛው ሁነን ፣ ፉከራም ልቅሶም ሲጠፋብን ካንተ በቀር ወደ ሕሊናችን የሚመልሰን ማነው?

አንዲት ቤተ ክርስቲያን አንድ እንድትሆን ፣ ሕመምና ልቅሶአችን ዳርቻ እንዲያገኝ እንማጸንሃለን! አማኑኤል ሆይ! በክንፍህ መዘርጋት አንተ ጋርደን ። ከልቅሶም ልቅሶ አለውና የቤተ ክርስቲያን ደጆች በምሕረት ይከፈቱልን ። እውነተኛው አዳኝ ክርስቶስ ሆይ ! አደባባይ የቆምህላት ቤተ ክርስቲያን አደባባይ ቆማለችና አንተ አስባት ! ለዘላለሙ አሜን !

ዲያቆን አሸናፊ መኮንን

በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም