መግቢያ » ልዩ ልዩ ሁለት » እንኳን 2015 ዓ.ም. የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ !

የትምህርቱ ርዕስ | እንኳን 2015 ዓ.ም. የጌታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጥምቀት በዓል በሰላም አደረሳችሁ !

የእርሱ የሆኑትን ሕዝቦች ፣ እረኝነቱ የሚያስፈልጋቸውን በጎች ፍለጋ አማኑኤል ወደ ዮርዳኖስ መጣ ። ንስሐ የሚገቡት የከበሩ መሆናቸውን ሊያሳይ የንስሐ ጥምቀት ወደሚጠመቁት ዘንድ ሄደ ። ከሁሉ የከበረ አገልግሎት ሰዎችን ለይቅርታና ለንስሐ ማብቃት መሆኑን ሊያሳይ ወደ ንስሐ ሰባኪው ወደ ዮሐንስ መጥምቅ ዘንድ ገሰገሰ ። በእውነት የምእመናን ቍጥር ሳይቀንስ በጥምቀቱ መታሰቢያ ቀን ይታያል ። ወትሮም ወደ እውነተኛዋ ዮርዳኖስ ወደ ቤተ ክርስቲያን ይመጡ ዘንድ ክርስቶስ ይጣራል ። ጎዳናውን የሚያጸዱ ቡሩካን ናቸው ፣ ክርስቶስ የሚያልፍበትን ልባቸውን ከቂም ከበቀል የሚያነጹ ጻድቃን ናቸው ። ብዙ ሕዝብ በጥምቀቱ መታሰቢያ ቀን ይታያል ። የተለያየ እንዲገናኝ ፣ ብቸኝነት “የሰው ያለህ” ያሰኘው በሕዝብ ግፊያ ፣ ሙቀትና ኃይል እንዲሰማው ጥምቀቱ አስተዋጽኦ ያደርጋል ።

ጭንቀት የሚሰማው እልል ሲልና እልልታ ሲሰማ የወጠረው ክፉ ስሜት ይበናል ። ሁሉም ሰው በየቤቱ ሆ ማለት ይችላል ። አደባባይ ወጥቶ ሆ የሚለው ለእግዚአብሔር ነው ። አምልኮቱ እንዳይቀር ፣ በዓሉና ባሕሉም እንዲጸና ቤተ ክርስቲያን ትመክራለች ። የእግዚአብሔር ቤት ሲሞላ ከማየት የበለጠ የሚያስደስት ምንም ነገር የለም ። ለዘመናት ጥበቃ የማያስፈልገው በዓል በዓለ ጥምቀት ነው ፤ ምክንያቱም ሁሉም ሕዝብ በአምልኮ ልብ ይወጣልና ማን ሊረብሽ ይችላል ! ይህ የአደባባይ በዓል ኢትዮጵያ በነጻነት የመኖርዋ ምልክት ነው ። ሃይማኖትም እንዲህ ባላገር ሁኖ በጎዳናው ሞልቶ መታየቱ ኢትዮጵያን ልዩ ያደርጋታል ።

የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ባለችበት ሁሉ በአንድ ቀን ፣ በተመሳሳይ ሰዓት ፣ በአንድ ዓይነት ዝማሬና ሥርዓት በዓሉ ይከበራል ። የአንዱ ደብር በዓል ከሌላው አይበልጥም ። በሃይማኖት ውድድር የለምና ።

ወዳጆቼ ሆይ ስሙኝ !

እናንተ እንዲህ ወደ ቤተ እግዚአብሔር ስትመጡ የአባቶችና የአገልጋይ ዲያቆናት ልብ በደስታ ይሞላል ። የእግዚአብሔር እንግዳ የሆናችሁትን እናንተን ለመቀበል ካህናት ይተጋሉ ። ታላቅ ቅንዓት ሊሰማን ይገባል ። የዛሬው ምእመን ነገም እንዲመጣ ፣ አምና ያለፈው ዘንድሮ ንስሐ እንዲገባ ፣ ቀጠሮ ያበዛው ቀጠሮውን ሰብሮ ሥጋና ደሙን እንዲበላ ቅንዓት ይሰማናል ።

በዓለ ጥምቀቱን የሰላም የደስታ ያድርግልን !

ይቆየን

ዲያቆን አሸናፊ መኰንን
ጥር 10 ቀን 2015 ዓ.ም.

በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም