መግቢያ » ግጥም » እግሬን ፈውስልኝ

የትምህርቱ ርዕስ | እግሬን ፈውስልኝ

                                                      አርብ፣ ጥቅምት 24 2004
ጎዳናው ሰፍቶብኝ መንገዱ በዝቶብኝ፣
የእግሮቼ አድራሻ መድረሻው ጠፍቶብኝ፣
ባገኘሁት ስዘልቅ በወደድሁት ስሮጥ፣
እግሮቼ መርተውኝ እዚም እዛም ስረግጥ፣
በአዘቅት በገደሉ በረግረጉ ስሰምጥ፣
ፍለጋህን ትቼ የእኔን መንገድ ስመርጥ፣
አንተ ግን ኢየሱስ፣
አይተህ አዝነህልኝ ደርሰህ ቆመህልኝ፣
በረግርግ ያለውን እግሬን አድንልኝ፣
ወጥመድ ይዞብኛል እባክህ ፍታልኝ፣
ጋሬጣ ወግቶብኛል እስኪ ፈውስልኝ፣
መንገድ ስቶብኛል የአንተን አሳይልኝ፣
ወደ ዓለም ኮብልሏል ወደ አንተ አቅናልኝ፡፡
ጉንድሽ ሆኖብኛል ሙሉ አድርግልኝ፣
አነክሶብኛል ዳሰህ አዘልልልኝ፣
በአንተ ዱካ ላይ ዳግም አራምድልኝ፣
ጉዞዬን እንድዘልቅ እግሬን ፈውስልኝ፡፡
ክርስቶስ ጌታ ሆይ ዛሬም ለዘላለም፣
የሄድክበት ሄጄ የቆምክበት እንድቆም፣
ስታርፍም አርፌ በሀገርህ እንድከትም፣
መንገድ መሪ ሆነህ ከፊት ለፊት ቅደም፡፡                                                                                                       
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም