መግቢያ » ግጥም » አልዕሉ አልባቢክሙ

የትምህርቱ ርዕስ | አልዕሉ አልባቢክሙ

ቅዳሴ ኤጲፋንዮስን የሚቀድሰው ካህን “አልዕሉ አልባቢክሙ” ማለት “ልቡናችሁን ከፍ ከፍ አድርጉ” በማለት ወደ ሰማይ ማደሪያ ምእመናንን ሲያነቃቃ ምእመናንም እንዲህ ብለው ይመልሱለታል ፡- “በአምላካችን በእግዚአብሔር ዘንድ አለን” ይሉታል ። በዚህ ጊዜ የእግዚአብሔርን ዘላለማዊ ባሕርይና ዘላለማዊ ብርታት ማወጅ ይጀምራል ።
እግዚአብሔር በገናንነቱ ገናና ነው ፤
በቅድስናውም የተቀደሰ ነው ፤
በምስጋናውም የተመሰገነ ነው ፤
በክብሩም የከበረ ነው ።
ከመቼ ወዲህ የማይሉት ቀዳማዊ ነው ፤
እስከ ዛሬ የማይሉት ማእከላዊ ነው ፤
እስከዚህ የማይሉት ደኃራዊ ነው ።
ለአነዋወሩ ጥንት የለውም ፤
ለአኳኋኑም ፍጻሜ የለውም ፤
ለዘመኑ ቊጥር የለውም ፤
ለዓመታቱም ልክ ቊጥር የለውም ፤
ለውርዝውናው ማርጀት የለበትም ፤
ለኃይሉም ጽናት ፣ ድካም የለበትም ፤
ለመልኩም ጥፋት የለበትም ።
ለጥበቡ ባሕር ፣ ድንበር የለውም ፤
ለትእዛዙም ይቅርታ ፣ መስፈርት የለውም ፤
ለመንግሥቱ ስፋት ፣ አቅም ልክ የለውም ፤
ለአገዛዙም ስፋት ፣ ወሰን የለውም ።
በኅሊና የማያገኙት ሥውር ነው ፤
በልቡናም የማይረዱት ምጡቅ ነው ፤
አእዋፋት የማይደርሱበት ረጅም ነው ፤
ዓሣዎች የማይዋኙበት ጥልቅ ነው ።
ከተራሮች ራስ ይልቅ ከፍ ከፍ ያለ ነው ፤
ከባሕር ጥልቅነት ይልቅ ጥልቅ ነው ፤
ነገሥታት የማይነሣሡበት ጽኑ ነው ፤
መኳንንት የማይቃወሙት አሸናፊ ነው ።
የጥበበኞችን ምክር የሚያጠፋ ጥበበኛ ነው ፤
የሚመክሩትን ሰዎች አሳባቸውን የሚያስረሳ ዐዋቂ ነው ፤
የጸኑ ልጓሞችን የሚፈታ ኃያል ነው ፤
የኃጥአንን ጥርሶች የሚያደቅ ፣
የትዕቢተኞችንም ክንድ የሚቀጠቅጥ ብርቱ ነው ።
የግብዞችን ፊት የሚያዋርድ ክቡር ነው ።
የዝንጉዎችን ብርሃን የሚያርቅ ከሃሊ ነው ።
ባልንጀራ የሌለው አንድዬ ነው ፤
ዘመድ የሌለው ብቸኛ ነው ፤
                    /ቅዳሴ ኤጲፋንዮስ ቊጥር 2-10/።
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም