እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ 2009 ዓ.ም የልደት በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ!
ፍጹም ክብር ካለበት ዓለም ፍጹም ውርደት ወዳለበት ምድር ለእኛ ሲል ተወለደ ፤ ባለ ወግ ሊያደርገን ባለ በረት ሆነልን ። ባለ ሰማይ ሊያደርገን ባለ መስቀል ተባለልን ። የኪዳን ቀለበት ሊያደርግልን በችንካር ቆሰለልን ። ነገሥታት ሊያደርገን የእሾህ አክሊል ደፋልን ፣ ካህናተ ጽድቅ ሊያደርገን ሐሰተኛ ተባለልን ። ሰማይና ምድር የማይችሉት በድንግል ማኅጸን አደረ ፤ በኪሩቤል ጀርባ የነገሠው በንጽሕት ድንግል እቅፍ ውስጥ አረፈ ። በዙፋኑ የሚጠብቀን እንደ ትንሽ ሕጻን ተሯሯጠ ። ሁሉ እንዲሆንልን ሁሉ የሌለው ሆነ ። የጌታችን እግሮች በረገጧት ምድር ላይ ስላላችሁ ደስ ይበላችሁ ። እርሱ ባለፈበት ሕይወት ስለምታልፉ እልል በሉ ። ኑሮ እንዳያሰጋችሁ ሕይወት ሆኖ ተወለደላችሁ ። በጊዜያዊው ነገር እጅ እንዳትሰጡ የዘላለሙን ፍስሐ አወረሳችሁ ። በእውነት እንኳን አደረሳችሁ! 
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም