የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ

የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ 
እንኳን ለጌታችንና ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ 2009 ዓ.ም የልደት በዓል በሰላምና በጤና አደረሳችሁ!
ፍጹም ክብር ካለበት ዓለም ፍጹም ውርደት ወዳለበት ምድር ለእኛ ሲል ተወለደ ፤ ባለ ወግ ሊያደርገን ባለ በረት ሆነልን ። ባለ ሰማይ ሊያደርገን ባለ መስቀል ተባለልን ። የኪዳን ቀለበት ሊያደርግልን በችንካር ቆሰለልን ። ነገሥታት ሊያደርገን የእሾህ አክሊል ደፋልን ፣ ካህናተ ጽድቅ ሊያደርገን ሐሰተኛ ተባለልን ። ሰማይና ምድር የማይችሉት በድንግል ማኅጸን አደረ ፤ በኪሩቤል ጀርባ የነገሠው በንጽሕት ድንግል እቅፍ ውስጥ አረፈ ። በዙፋኑ የሚጠብቀን እንደ ትንሽ ሕጻን ተሯሯጠ ። ሁሉ እንዲሆንልን ሁሉ የሌለው ሆነ ። የጌታችን እግሮች በረገጧት ምድር ላይ ስላላችሁ ደስ ይበላችሁ ። እርሱ ባለፈበት ሕይወት ስለምታልፉ እልል በሉ ። ኑሮ እንዳያሰጋችሁ ሕይወት ሆኖ ተወለደላችሁ ። በጊዜያዊው ነገር እጅ እንዳትሰጡ የዘላለሙን ፍስሐ አወረሳችሁ ። በእውነት እንኳን አደረሳችሁ! 
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ
አዳዲስ መጻሕፍትን ይግዙ

ተዛማጅ ጽሑፎች

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ