አንተ የነፍስ መልሕቅ ማዕበሉን አሳለፍከው !
አንተ ጽኑ መርከብ ከወደቡ አደረስከን !
አንተ ትጉህ እረኛ ከአውሬ ተናጠቅኸን !
አንተ የእውነት ፀሐይ ነጻ አወጣኸን !
አንተ የደናግል መመኪያ መጠሪያ ስም ሆንከን!
አንተ የካህን ካባ በአደባባይ አከበርከን !
አንተ የነፍስ ማረፊያ ልባችንን ደገፍክልን !
አንተ የቤታችን ራስ ጉድለትን ሞላህልን !
አንተ ሠራተኛ ተራራውን ደለደልክልን !
አንተ የድሀ አባት ሸለቆውን ሞላህልን !
አንተ የፍቅር ሀገር ሰው አዘጋጀህልን !
አንተ ብርሃን ሰባክያንን ላክልን!
አንተ ታሪክ አዳሽ እንደገና ፈጠርከን!
አንተ ታዳጊ ከምኞታችን አዳንከን!
አንተ ጥሩ ምንጭ ከመዛል አተረፍከን !
አንተ ነጭ ልብስ ከመራቆት አዳንከን !
አንተ የትኩዝ መጽናኛ በቃልህ ጠገንከን !
መድኃኔ ዓለም ሆይ!
አንተን የሚጠላ ያልታደለ ፣ ምስጋናህን የሚቃወም ቤቱ ወደ ሞት ያዘነበለ፤ ደምህን የሚያቃልል ዘላለሙን የበደለ ነው!
መድኃኔ ዓለም የሕይወት ሽታ ከዓይነ ሞት ሰወርከን !
ይህንንም ዘመን ሸፍነህ አሻግረን !
ተመስገን!
ሰኞ ሰኔ 29 ቀን 2018 ዓ.ም.