መግቢያ » ልዩ ልዩ ሁለት » የትውልድ ንስሐ

የትምህርቱ ርዕስ | የትውልድ ንስሐ

“አቤቱ ፥ መረመርኸኝ ፥ አወቅኸኝም ።” መዝ. 138፡1
በሽታ ሁሉ የሚርድልህ ፣ እባብና ጊንጥ በፊትህ የሚወድቅልህ ፣ የዓለሙ ሐኪም ፣ የዓለሙ ጤና እግዚአብሔር ሆይ አመሰግንሃለሁ ። በቃልህ መረመርኸኝ ፣ በማስተዋልህ አወቅኸኝ ። ሐኪም የተራቆተውን ታካሚ በር ዘግቶ ያየዋል ፣ አንተም ከልብስ ዘልቀህ አወቅኸኝ ። ሐኪም ቀዶ ጥገና አድርጎ ባለቤቱ ያላየውን የአካል ክፍሉም ያየዋል ፤ አንተም ልብና ኩላሊቴን መርምረሃል ። አዎ መረመርኸኝ ትኩሳቴ እንደ በዛ ፣ ደም ሳፈስስ ደሜ እንደ በዛ ፣ ስቆጣ ያንተን ፍርድ እንደረሳሁ አወቅኸኝ ። በርግጥ መረመርኸኝ አእምሮ እንደ ከዳኝ ፣ እኖራለሁ ብዬ ሰው እንደ ገደልሁ አወቅኸኝ ። በእውነት መረመርኸኝ ክርስቲያን ሁኜ ኑሬ ፣ ጎሠኛ ሁኜ ስሞት አወቅኸኝ ። በነፈሰበት እንደምነፍስ ፣ ያላጣራሁትን እንደ ማስተላልፍ ፣ ሕንፃ ሥላሴ ሰውን ለማፍረስ እንደምቸኩል መረመርኸኝ አወቅኸኝም ። ጽጌረዳን ስቆርጥ እንደምሳሳ ፣ ሰውን ስቆርጥ እንደምጨክን መረመርኸኝ አወቅኸኝም ። ያሳደግሁትን እንስሳ ለማረድ እንደምሳሳ ያሳደጉኝን ግን ለመግደል እንደምነሣ መረመርኸኝ አወቅኸኝም ። ልቤ ከድቶኝ ፣ አቅሌን ስቼ ፣ በቁመናዬ ልክ ወድቄ ፣ ሲኦልን ገነት አድርጌ መጥቻለሁና በቤትህ አሳርፈህ አክመኝ ። መረመርኸኝ አወቅኸኝም እባክህን መድኃኒት እዘዝልኝ ። እኔ የተበላሸሁ ነኝና ወደ ራሴ ሳይሆን ወዳንተ መልሰኝ ። ለዘላለሙ አሜን ።
ጥቅምት 19 ቀን 2012 ዓ.ም.
ዲአመ
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም