የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ

የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ 

የጽሑፍ ስብከቶች

የሚለውጥ ፍቅር – መግቢያ

የዲ/ን አሸናፊ መኰንን ገጽ ጥቅምት ፱፣፳፻፭ ዓ/ም ቀዳሚ ቃል በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን! በዓለም ላይ ከሚገኙት ኃይላት ይልቅ የፍቅር ኃይል ይበልጣል፡፡ ኃይል ጉልበትን ይገዛል፣ ፍቅር ግን ፈቃድን ይገዛልና ሁሉን የራሱ ያደርጋል፡፡ በዓለም ላይ ዕዳውን ሳያስመልስ የማይተኛ ነገር ቢኖር ፍቅር ነው፡፡ ይህም ፍቅር መለኮታዊ ወንዝ ነው፡፡ ድሆች ፍቅርን ይፈልጋሉ፤ ባለጠጎች ይበልጥ መወደድን ይሻሉ፡፡ እነርሱነታቸውን የሚወድ ሰው ያለ አይመስላቸውምና፡፡ እንኳን ለቆሙት ለሚያጣጥሩትም የሚያነቃ ኃያል ድምጽ አንድ ነው፡፡ « እግዚአብሔር ይወድሃል» እግዚአብሔር ማንንም ስለማይጠላ አይደለም የሚወደን፤ በተለየ ፍቅር ነው የሚወደን፡፡ አጠቃላይ የሰው ዘርን መውደድ ቀላል ነው፣ አንድን ሰው መውደድ ግን ከባድ ነው፡፡ እግዚአብሔር እያንዳንዳችንን ይወደናል፡፡ በትእዛዝ ማፍቀር አንችልም፤ እግዚአብሔር እንዴት እንደወደደን ስናውቅ ብቻ እንወደዋለን፣ እርሱንም ስንወድ ሌሎችን እንወዳለን፡፡ ኢየሱስ ክርስቶስ በኑሮውና በሞቱ የእግዚአብሔርን ፍቅር ገለጠ፡፡ ፍቅርን በሚዳሰስ አካል የተረከ ክርስቶስ ነው፡፡ አሊያም አካላዊ ፍቅር ክርስቶስ ነው፡፡ ደግ ለመሆን ምቹ ጊዜን የማይጠብቀው ይህ ፍቅር ሲገዛን መለወጥን እናገኛለን፡፡ ብዙ ሰዎች ክርስቲያንነትን የሚፈልጉት ገንዘባቸውን ለመቆጠብ፣ ከሚወራው በሽታ ለመዳንና ጨዋ ለመሆን ነው፡፡ የክርስትና ዓላማው ግን ግብረ ገብነት ሳይሆን ሕይወት ነው፡፡ ሕይወትን እንቀበላለን እንንቀሳቀሳለን፡፡ «የባሕርይ ለውጥ እናምጣ» እየተባለ ይነገራል፡፡ ሰዎችም አሳቡን አምነውበታል፤ ሊያደርጉት ግን አልቻሉም፡፡ ሰው ራሱን ለመለወጥ አምላክነት ያስፈልገዋል፡፡ ታዲያ ለውጡ ካስፈለገ ለውጡ የሚመጣው በማን ነው? «.

ተጨማሪ ያንብቡ »
ክምችት
ምድቦች