የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ

የዲያቆን አሸናፊ መኰንን ገጽ 

ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ ስለ አዲስ ዓመት ከሰበከው /1/

እንኳን ከዘመነ ማርቆስ 2010 ዓ.ም. ወደ ዘመነ ሉቃስ 2011 ዓ.ም. በሰላምና በጤና አሸጋገራችሁ !!
አዲሱ ዓመት መልካም የሚሆንላችሁ በዘመን መለወጫ ቀን መጠጥ ስለ ጠጣችአይደለም ። በተቃራኒው ዓመቱ መልካም የሚሆንላችሁ በዘመን መለወጫ ቀን (መስከረም አንድ) እና በተቀሩት ቀናት በእግዚአብሔር ዘንድ የታዘዙ ተግባሮችን ካደረጋችሁ ነው ። አንድ ቀን ከሌላ ቀን አንዳች አይለይምቀኖች መልካምና ክፉ የሚሆኑት ከራሳቸው ተፈጥሮ ሳይሆን ከኛ ቅንትና ስንፍና ነው ። የጽድቅን ሥራ ከራችሁ ቀኑ መልካም ይሆንላችኋል ። ኃጢአትን ከራችሁ (ቀኑ) ክፉና ስቃይ የሞላበት ይሆናል ። ስለ እነዚህ ነገሮች በጥልቀት ተመስጣችሁ ዕለት ለት እየጸለያችሁና ምዋት እየመወታችሁ ሙሉውን ዓመት እንደ መልካም ትመለከቱታላችሁ። ነገር ግን ስለ መልካም ምግባራት ግድ የለሽ ከሆናችሁ የነፍሳችሁንም እርካታ የወር መጀመሪያና የቀኖች ቊጥር ላይ ካደረጋችሁ መልካም የሆነውን ነገር ሁሉ ከራሳችሁ ታርቃላችሁ
መንፈሳዊ ጸሎት እንጂ አብዝቶ መጠጣት ፣ የተማርነው የእግዚአብሔር ቃል እንጂ ወይን ደስታን አይፈጥርም ። ወይን ሁከትን ያመጣል የእግዚአብሔር ቃል ግን እርጋታን ። ወይን ወደ ረብሻ ይወስዳል ቃለ እግዚአብሔር ግን ብጥብጥን ያርቃል ። ወይን መረዳትን ያጨልማል የእግዚአብሔር ቃል ግን የጨለመውን ያበራል ። ወይን አስቀድሞ ያልነበረ ጭንቀትንና ዘንን ያመጣል የእግዚአብሔር ቃል ግን የነበረውን (ጭንቀትና ፣ ዘን) ያርቃል። በክርስትናችን አስተምህሮ መረት የአሁኑን ነገር እንደ መናቅ ፣ የሚመጣውን ነገር በናፍቆት እንደ መጠበቅ ፣ ደንነትን ለማስጠበቅ አንዳችም ሰዋዊ ጉዳዮችን እንደ አለማሰብ እርካታንና ደስታን የሚሰጥ ነገር የለም ይህ ከሆነ (በዓመት አንድ ጊዜ ብቻ ሳይሆን) ሁልጊዜ በልን ማክበር ትችላላችሁ
ክርስቲያን በልን ማክበር ያለበት ለወራት ፣ ለአዲስ ዓመት ፣ ለጌታ ቀንም (ብቻ) አይደለም። በተቃራኒው ዘወትር በሐሕሐሐሐሐሐሐሐሐሐገገገይወቱ ለእርሱ የሚመጥነውን በል እንዲያከብር (ግድ ይለዋል) እንጂ ። (ለክርስቲያን) የሚመጥነው በል የቱ ነው? ጳውሎስ ሲናገር እንስማው፡- “በቅንነትና በእውነት ቂጣ በዓልን እናድርግ እንጂ በአሮጌ እርሾ በክፋትና በግፍ እርሾም አይደለም።” (1ኛ ቆሮ 5 8)
ንጹሕ ኅሊና ካለህ ዘወትር መልካም በሆኑ ተስፋዎች ተሞልተህ የሚመጡትን መልካም ነገሮች በመግለጥ በዓልን ታከብራለህ ። እነዚህንም ነገሮች በድፍረት ካላደረግሃቸው በብዙ ኃጢአቶችም ከወደቅህ እልፍ በሎች ቢኖሩም ከሚያዝኑ ሰዎች የተሻለ ሁኔታ ላይ አትሆ ። ነፍሴ በአሳብዋ ከጠለሸች ለእኔ የብሩህ ቀን ጥቅም ምንድር ነው ? ይህ ከሆነ ከአዲስ መት ጥቅምን ማግኘት የሚሻ ሰው ይህንን ያደርጋል ። ዓመቱ ሲጠናቀቅ ስትመለከቱ መታትን አሳልፏችኋልና ዘመንንምም አሻግሯችኋልና  ጌታን አመስግኑ ። የይወት ዘመናችሁን እየቆጠራችሁ ልባችሁን አጽኑ ራሳችሁንም እንዲህ በሉት፡- “ቀናት ያልፋሉ ዓመታት ይሞላሉ አብዛኛውን መንገድ ተጉዘናል እስካሁን ምን በጎ ነገርን አደረግን? እናደርገው ዘንድ መልካም ነገር ወዴት አለ? ከዚህ ከሁሉም ጽድቆች ባዶ ሆነንና ተራቁተን እንወሰዳለን ፍርም በደጅ ይጠብቀናል ። የቀረውም ይወታችን ወደ ሽምግልና ያደርሰናል
እነዚህነገሮች በአዲሱ ዓመት የመጀመሪያ ቀን በጥልቀት እያሰላሰልን በመመሰጥ መጪዎቹን ቀናት እናስብ ። ለአይሁዳውያን በነ፡- “ቀኖቻቸውም በከንቱ አለቁ ፥ ዓመቶቻቸውም በችኰላ ።” (መዝ 77(78)፥33) ተብሎ እንደ ተነገረላቸው አይደለም ። ይህ አስቀድሜ የተናገርኩት የማያቋርጠው ፣ ዓመታት በማለፋቸውም የማይዘገየው ፣ በቀናት የማይወሰነው ፣ ድውም ብታሙም በአንድ ይነት መንገድና አኳኋን የሚያከብሩት በዓል ነው ። እዚህ ላይ የጽድቅ ሥራ እንጂ ብት አያም ጊዜአዊ መግቦት አያስፈልግም ብት የለህምን ? ነገር ግን ከሁሉም ብቶች በላይ ፍሬያማ የሆነ ፣ የማይጠፋ ፣ የማይለወጥ አላቂም ያልሆነው ፈሪሃ እግዚአብሔር አለህ። ሰማያትን ፣ ሰማየ ሰማያትን ፣ ምድርን ፣ ባርን ፣ አየሩን ፣ ብዙ ዓይነት የሆኑትን እንስሳት ፣ እጅግ ብዙ የሆኑትን ጽዋትን ፣ የሰውን መላ ተፈጥሮ ተመልከት ! መላእክትን ፣ ሊቃነ መላእክትን ፣ በላይ ያሉትን ኃይላትን አስተውል ።እነዚህ ሁሉም የጌታህ ፍጥረቶች እንደሆኑ አስታውስ ። መጋቢ ሆነው ጌታ ባሪያ መሆን ፣ እርሱንም መጋቢህ ማድረግ እነዚህን ማግኘት ነው እንጂ ድህነት አይደለም ። ቀኖችን መጠበቅ የክርስትና አስተምህሮ ሳይሆን የሄለናውያን/የግሪካውያን/ የስህተት (ትምህርት) ነው  
እንደ ዜጋ በታጫችሁበት በላይኛዋ/በሰማያዊቷ ከተማ በዚያ ትታወቃላችሁ ። በዚያ ብርሃን ለጨለማ ድል ማይሰጥበት ፣ ቀን በሌሊት በማይተካበት በተቃራኒው ሁልጊዜ ቀንና ብርሃን በሚሆንበት ከመላእክት ጋር አንድ እንሆናለን ። ስለዚህ እነዚህን ነገሮች ያለ ማቋረጥ እንሻ ። (ሐዋርያው) እንዲህ ይላልና፡- “ክርስቶስ በእግዚአብሔር ቀኝ ተቀምጦ ባለበት በላይ ያለውን እሹ ።” (ቆላ 3፥1) ። የፀይ እንቅስቃሴ ዑደት ከሆነበት ቀንንም ከሚወልድበት ከምድር ጋር አንዳች አንድነት የላችሁም ። ነገር ግን በጽድቅ የምትኖሩ ከሆነ ሌሊቱ ቀን ይሆንላችኋል። በዝሙት ፣ በስካርና በሆዳምነት የሚኖሩት ቀናቸው ወደ ምሽትና ጨለማነት ይለወጣል ። ይህም የሚሆነው በፀይ መግባት ሳይሆን ልቡናቸው በስካር ስለሚጨልም ነው
እነዚህን ቀናት በጉጉት መጠበቅ  ፣ በቀናቱም ታላቅ የሆነን ደስታ መቀበል ፣ በማበርም ላይ መብራትን ማብራት ፣ አበባም መጎንጎን የልች (ዓይነት) ሞኝነት ነው ። እናንተ ግን እንዲህ ካለ ደካማነት ተላቃችሁ ጎልምሳችኋል ለሰማያዊቱ ከተማ ዜግነትም ታጭታችኋል ። ስለዚህ ግዙፍ የሆነ/በዓይን የሚታይ መብራት በማበር አታብሩ ነገር ግን በልባችሁ መንፈሳዊ ብርሃን ይብራ። መጽሐፍ እንዲህ ይላልና፡- “መልካሙን ሥራችሁን አይተው በሰማያት ያለውን አባታችሁን እንዲያከብሩ ብርሃናችሁ እንዲሁ በሰው ፊት ይብራ ።” (ማቴ 5፥16) [ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ “አባታችሁን ” ሳይሆን “አባታችንን ” ብሎ ይጠቀማል።]
ይህ መብራት ብዙ ሽልማትን ያሰጣችኋል። የቤተ መቅደሱን[1]በር አታስዉቡ ነገር ግን ከክርስቶስ እጅ የጽድቅ አክሊል እንድትቀዳጁ (መልካም) የሆነ አኗኗርን አሳዩ ። አንዳች ነገር በችኮላና በጥድፊያ አያም ቀለል ተደርጎ አይደረግ ። ስለዚህም ምክንያት ጳውሎስ እንዲህ ብሎ አዘዘ “እንግዲህ የምትበሉ ወይም የምትጠጡ ብትሆኑ ወይም ማናቸውን ነገር ብታደርጉ ሁሉን ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉት ።” (1ኛ ቆሮ 10፥31) [2]
ስትበሉ ወይም ስትጠጡ ለእግዚአብሔር ክብር አድርጉ ሲል ምን ማለት ነው? ድዎችን (በቤታችሁ) ጥሩ ፣ ክርስቶስን የማዕተካፋይ አድርጉ መብላትና መጠጣታችሁ ለእግዚአብሔር ክብር ይሆናል
ነገር ግን ለእግዚአብሔር ክብር እንድናደርግ የሚመክረን ይህን ብቻ ሳይሆን ሌሎች ነገሮችንም ነው ። ወደ ማበር መሄድና ቤት መቀመጥ እነዚህ ሁለቱ ለእግዚአብሔር ክብር ይደረጉ ። እነዚህ ሁለቱ ለእግዚአብሔር ክብር የሚሆኑት እንዴት ነው? ቤተ ክርስቲያን በምትመጡበት ፣ ጸሎት በምትካፈሉበት ፣ መንፈሳዊ ትምህርት በምትማሩበት ጊዜ ሁሉ ይህ ተግባር ለእግዚአብሔር ክብር ሁኗል
እንደገና ለእግዚአብሔር ክብር ቤት መቀመጥም አለ። ይህ እንዴት ይሆናል? (አንድ ሰው ቤት የመቀመጥ ተግባር በማድረጉ ብቻ እንዴት እግዚአብሔርን ያከብራል?) በማንኛውም ጊዜ ረብሻ በምትሰሙበት ፣ ሥርዓት የለሽነትንና ዲያብሎሳዊ ተግባር በምታዩበት ፣ ጉባኤው  ክፉና ርኩሳን በሆኑ ሰዎች ሲሞላ ቤት ተቀመጡ። ከዚህ ረብሻና ሥርዓት አልበኛነት ነሆናችሁ ለእግዚአብሔር  ክብር (ቤታችሁ) ተቀመጡ
ቤት መቀመጥና ከቤት መውጣት ለእግዚአብሔር ክብር ማድረግ እንደሚቻምስጋናና ተግሣጽንም ለእግዚአብሔር ክብር ማድረግ ይቻላል ። አንድ ሰው ለእግዚአብሔር ክብር ማመስገንና መገጽ ምንድር ማለት ነው? ይላል ። ብዙ ጊዜ በሥራ ቦታ ትቀመጣላችሁ ክፉና መጥፎ ሰው ሲያልፍ ትመለከታላችሁ ። ይህ ሰው የእብሪተኛነት ምልክት የሆነውን ቅንድቡን ወደ ላይ ከፍ አድርጎ በኩራት ተሞልቶ ብዙ ተከታዮችንና ሸንጋዮችን አስከትሎ ውድ የሆኑ ልብሶችን በመልበስ ፣ በኩራት መንፈስም ተከቦና በንፉግነት ሁሉን የራሱ በማድረግ ሲመላለስ ትመለከታላችሁ ። አንድ ሰው “ይህ ሰው አያስቀናምን ? የተባረከስ አይደለምን ?” ሲል ትሰማላችሁ ። ስለዚህ እናንተ (እንዲህ የሚለውን ሰው) ገጹት ። ዝም በል ፣ እዘን ንባህንም አፍስስ በሉት ። ስለ እግዚአብሔር ብሎ መገጽ ማለት ይህ ነው
“ይህ ሰው የተባረከ ያልሆነው ስለምንድር ነው?” የሚላችሁን ሰው እንዲህ በሉት ። እርሱ (የተባረከ የሆነው) ድንቅ የሆነ ፈረስ ፣ ወርቃማ ልጓም ፣ እጅግ ብዙ ባርያዎች ስላሉት ውድ ልብስ ስለሚለብስ በየቀኑም በስካርና በብት ስለሚኖር ነውን ? ነገር ግን በዚህ ምክንያት ክፉና የተረገመ ይሆና። ብዙ እንባም ያስፈልገዋል ። ይህ ከሆነ ስለዚህ ሰው አንዳች የምታደንቁት ነገር እንደሌለ ነገር ግን ውጫዊና የእርሱ ያልሆኑትን ነገሮችን ማለትም ፈረሱ፣ ልጓሙ፣ ልብሱብቻ ስታደንቁ ይታየኛል ።  ፈረሱ ፣ የፈረሱ ልጓም ፣ የልብሱ ውበት ፣ የባሪያዎቹም ንካሬና ኃይል እነዚህ ሁሉ ሲደነቁ ነገር ግን እርሱ ሳይመሰገንና ሳይደነቅ ሲያልፍ ከዚህ በላይ የሚያሳዝን ምን ነገር እንዳለ እስኪ ንገሩኝ ? ከዚህ ሰው በላይ ምስኪን ማን አለ? አንዳች የራሱ መልካም የሚባል ነገር ፣ አልያም ከዚህ ይዞት የሚሄደው አንዳች ነገር የሌለው ነገር ግን ሙሉ በሙሉ ውጫዊ በሆኑ ነገሮች ከሚመሰገንና ከሚደነቅ (ከዚህ ሰው በላይ ምስኪን አለን?) ። የእኛ የሆኑ ማጌጫዎችና ብቶች የነፍስ መልካምነት ፣ የጥሩ ምግባር ብትና በእግዚአብሔር ላይ ያለ መታመን ናቸው እንጂ ባሪያዎች ፣ ልብስና ፈረስ አይደሉም
እንደ ገና ሌላ (ሰው እናስብ ። ይህ ሰው) የኔ ቢጤ ፣ የተጣለ ፣ የተናቀ ሕይወቱንም በድህነት የሚያሳልፍ መልካም ምግባርም ያለው በወዳጆቹም ዘንድ እንደ ኀዘነተኛ የሚቆጠሩ ሰው ነው ። ይህ ሰው አመስግኑት ፤ የዚህ  ሰው ኑሮ ጠቃሚና መልካም የሆነ የይወት መንገድ ተግጽና ምክር ነው ይህ ሰው ምስኪንና አሳዛኝ ነው ካሉ ይህ ሰው እግዚአብሔር ወዳጁ ስለሆነ ፣ ይወትንም በመልካምነት ስለሚኖር ፣ የማይጠፋም ንብረት ባለቤት ስለሆነ ንጹሕ ኅሊናም ስላለው ከሁሉም በላይ የተባረከ ነው በሏቸው ። ይህ ሰው ሰማይንና የሰማይን መልካም ነገሮች የሚወርስ ሆኖ ሳለ (ቁሳዊ) ብት ስለሌለው ምን ይጎዳል ? እናንተ ራሳችሁ በዚህ መንገድ ካሰባችሁ[3] ሌሎችንም ካስተማራችሁ ሁለቱንም ለእግዚአብሔር ክብር በማድረግ ከማመስገንም ከመገሰጽም ከሁለቱም ታላቅ ሽልማትን ትቀበላላችሁ ። እኔም እነዚህን በማለት ስሜታችሁን በከንቱ አልስብም ነገር ግን እንዲህ ያለውን ነገር ለማድረግ ለቆረጡ ሰዎች ታላቅ የሆነ ሽልማት በእግዚአብሔር ዘንድ እንዳለ እናገራለሁ ። ስለ እነዚህ ነገሮች ማለትም ክትን የሚሩ እንደሚናቁ እግዚአብሔርንም የሚፈሩ እንደሚከብሩ ነዩ እንዴት በግልጽ እንዳስቀመጣቸው ተመልከቱ


[1]Do not crown the door of the house የሚል ሲሆን የቤተ መቅደሱን የሚለው የተጠቀምኩት ከላይ በቤተ መቅደስ ሥርዓቶች እየተናገረ ስለነበረ ነው። መብራት አበባ…….
[2] ከዚህ በኋላ ያለው ስብከት ጭብጥ መልእክት በዚህ ጥቅስ ላይ የተመረኮዘ ነው።
[3] Philosophize 
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ
አዳዲስ መጻሕፍትን ይግዙ

ተዛማጅ ጽሑፎች

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ