መግቢያ » ግጥም » አትፈር አትፍራ

የትምህርቱ ርዕስ | አትፈር አትፍራ

                    
                                ቤተጳውሎስ፤ እሁድ ሚያዚያ 21 2004 ዓ.ም.
 አታመንታ ቀኝ ግራ
በሞተልህ ልትኮራ
ክርስቶስን ልትጠራ
አትደንግጥ አትሸበር
ተወልደሀልና ከማይጠፋ ዘር
ምንድር ነው መርበትበት
ጭንቀትና ሥጋት?
አይከፈል አቅልህ ፅና በክንዶቹ
ልብህ አይናወጥ ታይተሃል በአይኖቹ
በመንፈስ ተቃጥለህ በትክክል ጥራው
ምስጋና አምልኮ ለርሱ ብቻ ስጠው 

                መስክርለት በሕይወት መንፈሱ ካንተ ነው

ማንም አይችልህም ተዋጊህ እርሱ ነው
የሌጌዎን ጭፍራ ሞገዱን አትፍራ
ለእርሱ በመኖርህ መቶ እጥፍ እንጂ የለውም ኪሣራ
ከፍ አድርገው ስሙን ጮኽህ ተናገረው
ያለ የነበረ የሚኖር ሕያው ነው
አትፍራ አትደንግጥ ሩጥ በብዙ ትምክህት
አይቀርቡም ወዳንተ የአጋንንት ሠራዊት
ከብረት ጋሻ ይልቅ ይመክታል ስሙ
ተግተህ ተዋጋ እንጂ አታስብ ለድሉ
በክብር መሞቱ ሞገስ ነው አትፍራ
ነብስ የሚቀጣውን እርሱን ብቻ ፍራ
ተጓደድ በስሙ አትታወክ በርታ
የቆምክባት ዓለት ነውና አለኝታ
አትፈር አትፍራ ኢየሱስ ነው ጌታ  
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም