መግቢያ » ግጥም » የምስጋናዬ ድምፅ

የትምህርቱ ርዕስ | የምስጋናዬ ድምፅ

                                                                                            አርብ፣ መስከረም 26 2004

ይገባዋል ለርሱ የምስጋና ነዶ
አድኖኛልና ከዙፋኑ ወርዶ
እርሱ ነው ጌታዬ እርሱ ነው አምላኬ
በደሙ ተፎ አበራ ታሪኬ
ሲያንሰው ነው ስግደቱ ያንሰዋል እልልታ
ሞትን በሞቱ ይል በድንቅ ለረታ

ምስጋና በፊቱ ይደረብለታል
የእልልታ ቅኔ ዙፋኑን ይሞላል
ይጨመርለታል የአምልኮ ስግደት
ለነፍሴ መናናት ሆኗታል በረከት
የዝማሬው ቅኔ እንደ ው ይፍሰስ
ተለውጫለሁኝ በልቤ መታደስ
አጨበጭባለሁ ነፍሴ በእርሱ ረክታ
ይደረብ ይጨመር ይብዛለት እልልታ
የምስጋና ነዶ እፊቱ ይከመር
ለነፍሴ ድቋ ነው ያሉ እግዚአብሔር
አመለኩት እርሱን ተገዛሁ በነፍሴ
ታላቅ ጥቅሜ ሆኗል ለርሱ መቀደሴ
በልጁ ደም ረጭቶ በመረቀው መንገድ
ታምኜ እጓዛለሁ በበጉ መታረድ
የወደቀው ጠላት በኔ ላይ ሀይል አጥቷል
የልጁ ደም ጋርዶኝ አርነቴ ታውቋል
ሐፍረቴ ተወስዷል ውድቀቴ ተሽሯል
በኢየሱስ ጌትነት ታሪክ ተለውጧል፡፡
እረማመዳለሁ በነጻነት መንገድ
በፍቅሩ ወላፈን ልቤ ፍሞ ይንደድ
እዘምራለሁኝ በደስታ ሲቃ
በሆነልኝ ነገር ነፍሴ ትነቃቃ
ይኸው ነው በእርሱ የመመረጥ
አረፍኩ ተቀመጥኩኝ በጌታ ፍቅር ውስጥ
የምስጋናዬ ድምጽ ወደ ላይ ይሰማ
የበረከት ትርፉ
           የመክበሬም ትርጉም
                      ሩ ነውና፡፡

በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም