መግቢያ » ልዩ ልዩ አንድ » የሰማይ ድምፅ » ሲያስቡን እንዲደሰቱ

የትምህርቱ ርዕስ | ሲያስቡን እንዲደሰቱ

 “በጸሎታችን ጊዜ ስለ እናንተ ስናሳስብ፥ የእምነታችሁን ሥራ የፍቅራችሁንም ድካም በጌታችንም በኢየሱስ ክርስቶስ ያለውን የተስፋችሁን መጽናት በአምላካችንና በአባታችን ፊት ሳናቋርጥ እያሰብን ፥ እግዚአብሔርን ሁልጊዜ በሁላችሁ ምክንያት እናመሰግናለን” 1ተሰ. 1፡2-3
ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ በተሰሎንቄ አማኞች ውስጥ ያገኘውን መልካም ነገር በአድናቆት እየገለጠ ነው ። ሰዎች ክፉ ሥራቸውን ስንገልጥላቸው እንዲተዉት ሲሆን መልካም ሥራቸውን ደግሞ እንዲያበረቱት መንገር ያስፈልጋል ። ሰዎች የጎደላቸውን ነገር ከመናገራችን በፊት ያላቸውን መልካም ነገር መንገር በጣም ወሳኝ ነው ። ክስና ወቀሳ ሁለቱም አንድን ስህተት የሚናገሩ ሲሆን ዓላማቸውና አቀራረባቸው ግን ተለየ ነው ። ስለዚህ ወቀሳ የመንፈስ ቅዱስ ፣ ክስ ደግሞ የሰይጣን ነው እንላለን ። ሐዋርያው ጴጥሮስን ያገኘው መንፈስ ቅዱስ ሲሆን ይሁዳን ግን ሰይጣን አገኘው ። የሰዎችን መልካም ሥራቸውንና ሰብእናቸውን ማድነቅ ውዳሴ ከንቱ አይደለም ። ውዳሴ ከንቱ ተቀባዩ ይገባኛል ብሎ ሲቀበለውና ሰጪው ደግሞ በምስጋና አደንዝዞ ለመዝረፍ ሲጠቀምበት የሚመጣ ስህተት ነው ።
ዴማስን ከጥሪው ባስቀረችው ተሰሎንቄ ክርስቶስ ዛሬ እንደሚመጣ ሁነው የሚኖሩ ምእመናን መገኘታቸው ድንቅ ነው ። አዳም የበደለው በገነት ውስጥ ሲሆን ሎጥ ግን የተቀደሰው በሰዶም ነው ። ደቀ መዝሙሩን ባስቀረችው ተሰሎንቄ ምእመናን ደግሞ አሸነፉባት ። ሐዋርያው የተሰሎንቄን ምእመናን በጸሎት ያስባቸው ነበር ። ያዘመትናቸውን ምእመናን በጸሎት ስናስባቸው ድል የእነርሱ ይሆናል ። ከመድረክ ስንወርድ በጸሎት ማገልገልን መርሳት የለብንም ። ሙሴ ኢያሱንና ጎልማሶችን አማሌቅን ለመውጋት አሰማራና እርሱ ግን በተራራ ላይ ሁኖ ይጸልይ ነበር ። /ዘጸ. 17፡8-13/ ሐዋርያው የተሰሎንቄን አማኞች መልካምነታቸውን እንዲያጸናላቸው በጸሎት ያሳስብ ነበር ። የሰዎችን መልካምነት በጣም እያጋነንን ስናወራ ጠላት እናበዛባቸዋለን ። ስንጸልይላቸው ግን እንከልላቸዋለን ።
የተሰሎንቄ ምእመናን የእምነት ሥራ ነበራቸው ። እምነታቸው የመመጻደቅ ፣ ጸድቄአለሁ ብሎ የመኩራራት አልነበረም ። እምነታቸው ፍሬ ነበረው ። በመቀጠልም “የፍቅራችሁን ድካም” ይላል ። ፍቅር ድካም አለው ። አንድን ሰው ስንወድ ዋጋ እንከፍላለን ። ዋጋ የማይከፍልና ዋጋ ለመክፈል የማይፈልግ አፍቃሪ መሆን አይችልም ። ሐዋርያው በጌታችን በኩል ያለውን የተስፋቸውን መጽናት ያደንቃል ። ምእመናኑ ተስፋቸው ክርስቶስ እንጂ ሌላ አልነበረም ። በዚህም ተስፋ ጸኑ እንጂ አማራጭ አልፈለጉም ። ለሐዋርያው የምስጋና ርእስ ሁነውለት ስለ እነርሱ እግዚአብሔርን ያመሰግናል ። ሕይወታችን በጎ ሲሆን ለብዙዎች ይበልጥ ለመንፈሳውያን አባቶቻችን የምስጋና ርእስ እንሆናለን ።
ያለሁበት አገር ለመንፈሳዊነት አይመችም ካላችሁ የተሰሎንቄ ምእመናንን አስቡ ። አገልጋዩ እየበደለ እኔማ የምትሉ ዴማስ ኮብልሎ የጸኑትን ሰዎች አስቡ ። እምነታችሁ ሥራ የሌለው እንዳይሆን በድን ወይም ሙት እምነትን አስወግዱ ። ፍቅራችሁ ድካም የማይፈልግ ከሆነ የፍቅርን አገር ማግኘት አትችሉም ።
ጌታ ሆይ ልቤን ባንተ ፍቅር ጥመደው ። የሚመሰክር ሕይወት ስጠኝ ። ተስፋን ጥዬ እንዳልባዝን አግዘኝ ። ለዘላለሙ አሜን ።
የሰማይ ድምፅ 1
ሐምሌ 24 ቀን 2011 ዓ.ም.
ዲ.አ.መ.
በማኅበራዊ ሚዲያ ያጋሩ
ፌስቡክ
ቴሌግራም
ኢሜል
ዋትሳፕ

ተዛማጅ ትምህርቶች

የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ
የትምህርቱ ርዕስ

መጻሕፍት

በዲያቆን አሸናፊ መኰንን

በTelegram

ስብከቶችን ይከታተሉ

አዳዲስ መጻሕፍት

ትርጉሙ:- ቀይ ዕንቈ

ለምድራችንና ለአገልግሎታችን በረከት የሆነ መጽሐፍ
የመጀመሪያ እትም ጥቅምት 2016 ዓ.ም

1ኛ ጢሞቴዎስ ትርጓሜ – ክፍል አንድ

የመጀመሪያ እትም ሐምሌ 2013 ዓ.ም

ምክር አዘል መጽሐፍ

የመጀመሪያ እትም